የደደቢት ቀጣዩ አሰልጣኝ የውጭ ዜጋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል
ደደቢት የውጭ ዜጋ አሰልጣኝ ለመቅጠር እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ ክለቡ የፖላንድ እና የፔሩ ዜግነት ያላቸው አሰልጣኞችን ሲቪ እየተመለከተ ሲሆን ከሁለቱ አንዱ የክለቡን ፍላጎት የሚያሟሉ ከሆነ ለሰማያዊው ጦር ይፈርማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ክለቡ ከአሰልጣኝ ቅጥር ጋር በተያያዘ ሃገር ውስጥ ያሉ አሰልጣኞችን ሊቀጥር የሚችለው ከውጭ ሊያመጣቸው ያቀዷቸው አሰልጣኞች ካልተሳኩ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ እ4ስካሁን የ2 የሃገር ውስጥ አሰልጣኞችን ወረቀት እየተመለከቱ እንደሆነም ታውቋል፡፡
ክለቡ ከተጫዋቾች ዝውውር ጋር በተያያዘ እስካሁን ተጫዋቾችን ማስፈረም እንዳልጀመረ ከክለቡ ህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ደደቢት ነገ እና ረቡእ የተጫዋቾቹን ኮንትራት የማደስ እንቅስቃሴ እንደሚጀመር የተገለፀ ሲሆን የወጣቱ ተከላካይ አስቻለው ታመነን ኮንትራት ለማራዘም በቃል ደረጃ ከስምምነት መድረሳቸው ታውቋል፡፡ ከራምኬል ሎክ ጋር ስሙ በከፍተኛ ደረጃ የተያያዘው ደደቢት ከተጫዋቹ ጋር እስካሁን ምንም ድርድር እንዳላደረገም አስታውቋል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...