የብሄራዊ ሊግ የምድብ ጨዋታ ዛሬ ይጀመራል


ወደ 2007 የኢትዮጰያ ፕሪሚየር ሊግ ለማለፍ የሚደረጉ ጨዋታዎች ዛሬ በባህር ዳር ስታድየም ይጀመራሉ፡፡ ውድድሩን የምታስናግደው ባህርዳር ከተማ 16 ክለቦችን ተቀብላ ያጠናቀቀች ሲሆን ዛሬ በመክፈቻ ስነ-ስርአቱ ለየዞኑ አሸናፊዎች ሽልማት በመስጠት ውድድሩ ይጀመራል፡፡

ከ7ቱ ዞኖች በአሸናፊነት ያጠናቀቁት ሱሉልታ ከነማ (ከማእከላዊ ሀ) ፣ አ.አ. ፓሊስ (ከማእከላዊ ለ) ፣ ባህርዳር ከነማ (ከሰሜን ሀ) ፣ ወልዲያ ከነማ (ከሰሜን ለ) ፣ ሻሸመኔ ከነማ (ከደቡብ ሀ) ፣ ሆሳእና ከነማ (ከደቡብ ለ) እንዲሁም አዳማ ከነማ (ከምስራቅ) ዋንጫ ይቀበላሉ፡፡

የምድብ ድልድሉ ትላንት 9 ሰአት ላይ ይፋ የሆነ ሲሆን በአራት ምድብ የተከፈለው የምድብ ድልድል ይህንን ይመስላል፡፡

ምድብ– 1
.
ባህርዳር ከነማ
.
አዳማ ከነማ
.
ልደታ ኒያላ
.
ቡራዩ ከነማ

ምድብ – 2
.
ጥቁር አባይ
.
ሻሸመኔ ከነማ
.
ወልቂጤ ከነማ
.
አዲስ አበባ ፖሊስ

ምድብ– 3
.
ፋሲል ከነማ
.
ሆሳህና ከነማ
.
ድሬድዋ ከነማ
.
ሱሉልታ ከነማ

ምድብ– 4
.
ወልድያ ከነማ
.
አዲስ አበባ ከነማ
.
ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት
.
ደቡብ ፖሊስ

ውድድሩ ዛሬ በአስተናጋጁ ከተማ ክለብ ባህርዳር ከነማ እና አዳማ ከነማ መካከል 9፡00 ላይ በሚደረግ ጨዋታ ይጀምራል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *