የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሀምሌ 7 ልምምድ ይጀምራል
ኢትዮጵያ በ2015 በሞሮኮ ለሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የማጣርያ ጨዋታዋን ነሀሴ 29 ቀን 2006 አም. በአዲስ አበባ ስታድየም ከአልጄርያ ጋር በምታደርገው ጨዋታ ትጀምራለች፡፡ ለጨዋታው 2 ወራት የቀሩት ሲሆን ብሄራዊ ቡድኑም ዝግጅቱን ከሀምሌ 7 ጀምሮ ያካሂዳል፡፡
አሰልጣኝ ማርያኖ ባሪቶ ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በቱርክ እና በሆላንድ ዝግጅት ለማድረግ እንዳሰቡ መናገራቸው የሚታወስ ሲሆን በመጀመርያ ከተመረጡት 38 ተጫዋቾች መካከል 7 ተጫዋቾችን ቀንሰው 1 ተጨማሪ ተጫዋች ከ20 አመት በታች ቡድኑ መርጠዋል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ታዳጊ ናትናኤል ዘለቀ በአዲሱ ምርጫ የተካተተ ሲሆን ዳዊት ፍቃዱ ፣ አሰግድ አክሊሉ ፣ ማታይ ሉል ፣ ታፈሰ ሰለሞን ፣ ሮቤል ግርማ ፣ ኤፍሬም አሻሞ እና ሽመክት ጉግሳ ተቀንሰዋል፡፡
የ32ቱ ተጫዋቾች ዝርዝር የሚከተለው ነው፡፡
ግብ ጠባቂዎች (3)
ጀማል ጣሰው (ቡና) ፣ ታሪኩ ጌትነት (ደደቢት) ፣ ሲሳይ ባንጫ (ደደቢት)
ተከላካዮች (10)
አሉላ ግርማ ፣ ቢያድግልኝ ኤልያስ ፣ ሳላዲን በርጊቾ ፣ አበባው ቡታቆ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ፣ ብርሃኑ ቦጋለ ፣ አክሊሉ አየነው ፣ ስዩም ተስፋዬ (ደደቢት) ፣ ቶክ ጄምስ (ኢትዮጵያ ቡና) ፣ ሽመልስ ተገኝ (መከላከያ) ፣ ግርማ በቀለ (ሀዋሳ ከነማ)
አማካዮች (14)
ምንያህል ተሸመ ፣ አዳነ ግርማ ፣ አንዳርጋቸው ረታ ፣ ናትናኤል ዘለቀ ፣ በኃይሉ አሰፋ ፣ ምንተስኖት አዳነ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ፣ ዳዊት እስጢፋኖስ ፣ ጋቶች ፓኖም ፣ አስቻለው ግርማ ፣ መስኡድ መሃመድ (ቡና) ፣ ታደለ መንገሻ (ደደቢት )፣ ሽመልስ በቀለ (ክለብ የለውም) ፣ አስራት መገርሳ (ዳሽን) ፣ አዲስ ህንፃ (አህሊ ሼንዲ)
አጥቂዎች (5)
ኡመድ ኡኩሪ ፣ ፍጹም ገብረማርያም (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ፣ ሳላዲን ሰኢድ (ዋዲ ዴግላ) ፣ ጌታነህ ከበደ (ቢድቬትስ ዊትስ) ፣ ፍቅሩ ተፈራ (ክለብ የለውም)
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating