ብሄራዊ ሊጉ ነገ በሚደረጉ 6 ጨዋታዎች ይቀጥላል
ትናንት የተጀመረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሊግ የምድብ ጨዋታ ነገ በሚደረጉ 6 ጨዋታ ይቀጥላል፡፡ ከፍተኛ ግምት የተሰጣቸው ጨዋታዎችም ይካሄዳሉ፡፡
በምድብ 2 የሚገኙት ክለቦች ነገ በሳቢያን ሜዳ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ፡፡ ጠዋት 3፡00 ላይ ናሽናል ሴሚንት ከጅማ አባቡና ጋር የእለቱን የመጀመርያ ጨዋታ ሲያደርጉ ቀጥሎ ደግሞ በ5፡00 ደግሞ ሻሸመኔ ከነማ ከሱሉልታ ከነማ ጋር ይፋለማሉ፡፡ አዲስ አበባ ከነማ ባቱ ከነማን የሚገጥምበት የምድቡ የእለቱ የመጨረሻ ጨዋታ 10፡00 ላይ ይካሄዳል፡፡
በምድብ 4 የሚደረገው ጨዋታ በድሬዳዋ ስታድየም ይካሄዳል፡፡ በ2007 የብሄራዊ ሊግ የዞኖች ውድድር ላይ በግሩም አቋም ምድባቸውን በበላይነት ያጠናቀቁት ደቡብ ፖሊስ እና መድን የምድቡን ትልቅ ጨዋታ ነገ በ4፡00 ይካሄዳል፡፡ የሁለቱን ጨዋታ ተከትሎ በ8፡00 የኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት ከ ወሎ ኮምቦልቻ ይፋለማሉ፡፡ በ10፡00 ደግሞ አማራ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት (አውስኮድ) ከ ሆሳእና ከነማ ይጫወታሉ፡፡
(ዳንኤል መስፍን – ድሬዳዋ)
ተዛማጅ ፅሁፎች
ሀዲያ ሆሳዕና የዕግድ ውሳኔ ተላለፈበት
ሀዲያ ሆሳዕና ከዚህ ቀደም በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተሰጠበትን ውሳኔ ተግባራዊ አላደረገም በሚል የዕግድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ለ15 ተጫዋቾች...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...