ብሄራዊ ሊግ ፡ ሁለቱ ወሳኝ ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሰአት ይደረጋሉ
የብሄራዊ ሊጉ የውድድር እና ስነስርአት ኮሚቴ ነገ የሚደረጉት ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሰአት እንደሚካሄዱ ቢገልፅም ከአንድ ሰአት በፊት ደግሞ አላፊውን የሚለዩት 2 ጨዋታዎች ብቻ በተመሳሳይ ስታድየም እንደሚደረጉ አስታውቋል፡፡
በዚህም መሰረት ፡-
03፡00 – ድሬዳዋ ከነማ ከ ፋሲል ከነማ – ድሬዳዋ ስታድየም
03፡00 – ፌዴራል ፖሊስ ከ አርሲ ነገሌ – ሳቢያን ሜዳ
05፡00 – ወልዋሎ ከ ቡራዩ – ድሬዳዋ ስታድየም
-የውድድር እና ስነስርአት ኮሚቴው በወሰነው ውሳኔ መሰረት ነገ የማለፍ እድል ያላቸው ክለቦች በተመሳሳይ ሰአት ሲጫወቱ አስቀድመው ከውድድሩ መሰናበታቸውን ያረጋገጡት ወልዋሎ እና ቡራዩ ከነማ በ5፡00 በድሬዳዋ ስታየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ የሌሎቹ ምድቦች ጨዋዎች ግን በሶስቱ ሜዳዎች በተመሳሳይ ሰአት ይደረጋሉ፡፡
-ሳቢያን/መከላከያ ሜዳ የሚደረገው ጨዋታ ከተቋረጠ በድሬዳዋ ስታድየም የሚደረገውም ጨዋታ እንዲቋረጥ ይደረጋል፡፡
-ጨዋታዎቹ ጠዋት እዲሆኑ የተወሰነው ምናልባት ጨዋታው ቢቋረጥ/ባይደረግ ሁኔታዎችን አመቻችተው ከሰአት ለማጫወት እንዲመች እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
-በተመሳሳይ ሰአት የሚደረጉት ጨዋታዎች የሚደረግባቸው ሜዳዎች የተለዩት በእጣ ነው፡፡
-የውድድር እና ስነስርአት ኮሚቴው እንዳስታወቀው ሌሊቱን በሳቢያን ሜዳ ዝናብ የሚዘንብ ከሆነ ጨዋታው በመከላከያ ሜዳ ይደረጋል፡፡
-የየምድቡ የመጨረሻ ጨዋታዎች በየቀኑ ተደርገው ሰኞ ወደ ሩብ ፍፃሜ የሚያልፉት ቡድኖች ሙሉ ለሙሉ ይታወቃሉ፡፡ በዚህም መሰረት ቅዳሜ የምድብ 2 ፣ እሁ8ድ የምድብ 3 እንዲሁም ሰኞ የምድብ አራት የመጨረሻ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ፡፡
-ውድድሩ ለ2 ቀናት እረፍት ያደርግና የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ከሀሙስ ጀምሮ ይካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating