ሳምሶን አየለ ለዳሽን ቢራ አሰልጣኝነት ጫፍ ደርሷል
ባለፈው ሳምንት ዳሽን ቢራ እና አሰልጣኝ ታረቀኝ አሰፋ ስምምነት ላይ ቢደርሱም ሀዋሳ ከነማ በመሃል ጣልቃ ገብቶ ቅሬታ በማሰማቱ የታረቀኝ የዳሽን ጉዞ መስተጓጎሉ ይታወሳል፡፡ አሁን በክለቡ ቀሪ ኮንትራት ያለው ታረቀኝ አሰፋ በሀዋሳ ከነማ የመቆየቱ ጉዳይ እርግጥ እየሆነ መጥቷል፡፡
ዳሽን ቢራ የታረቀኝን መቅረት ተከትሎ የቀድሞው የሐረር ሲቲ አሰልጣኝ ሳምሶን አየለን በዋና አሰልጣኝነት ለመሾም ለስምምነት መድረሳቸውን ዛሚ ስፖርት ብሄራዊ ዘግቧል፡፡
ሳምሶን አየለ ዳሽን ቢራን ለ2 አመታት ለማሰልጠን የተስማሙ ሲሆን ያለቀውን የውድድር ዘመን በዋና አሰልጣኝነት የጨረሱት ካሊድ መሃመድ የሳምሶን ረዳት ሆነው ይቀጥላሉ፡፡
የቀድሞው የእርሻ ሰብል ተጫዋች ሳምሰሶን አየለ በ2004 ክረምት ሐረር ሲቲን ለረጅም ጊዜ ያሰለጠኑት አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነ ማርያም ወደ ኢትዮጵያ ቡና ማምራታቸውን ተከትሎ በክለቡ ዋና አሰልጣኝነት የተሸሙ ሲሆን በ2006 አጋማሽ በጤና ችግር ምክንያት ስራቸውን እስከለቀቁበት ጊዜ ድረስ የምስራቁን ክለብ በዋና አሰልጣኝነት መርተዋል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating