የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አንጎላን ይገጥማል
ዋሊያዎቹ የአንጎላ አቻቸውን በሚመጣው እሁድ ሉዋንዳ ላይ ይገጥማል፡፡ ዋሊያዎቹ በሀዋሳ ሲደርጉት የነበረውን ጠንካራ ልምምድ አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ የተመለሱ ሲሆን ረቡእ እለት ወደ ሉዋንዳ የሚያቀኑ ይሆናል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ከአንጎላ አቻው ጋር ከተጫወተ በኅላ ወደ ብራዚል በማቅናት ከ5 ክለቦች ጋር ጨዋታ እንደሚያደርግ የፌድሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ጁነይዲ ባሻ በትዊተር ገፃቸው ገልፀዋል፡፡ አቶ ጁነዲ በተጨማሪም ከግብፅ እና ቤኒን ብሄራዊ ብድኖች የቀረበላቸውን የወዳጅነት ጨዋታ ከግዜ መጣበብ ጋር ያልተቀበሉት ሲሆን ከግብፅ ጋር የመጫወት እድሉ አሁንም አንዳለ ግን ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ከአንጎላ ጋር እና ከተለያዩ የብራዚል ክለቦች ጋር ለመጫወት መወሰኑ ከአንዳንድ የስፓርት ቤተሰብ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ አሁንም ከአልጄሪጋር ተቀራራቢ የጨዋታ ስልት ካላት ግብፅ ጋር መጫወቱን ምርጫ እንደሚያደርጉ አንዳንድ የዋሊያዎቹ ደጋፊዎቹ ጠቅሰዋል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating