ኢትዮጵያ ከሲሸልስ ነጥብ ተጋራች
ሲሸልሽ እና ኢትዮጵያ በቪክቶርያ ዩኒቲ ስታድየም ባደረጉት የምድብ 10 ሁለተኛ ጨዋታ 1-1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡
በጨዋታው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰላለፍ ይህንን ይመስል ነበር፡-
ታሪክ ጌትነት
ስዩም ተስፋዬ (በ54ኛው ደቂቃ ግብ አስቆጥሯል) ፣ ዋሊድ አታ ፣ አስቻለው ታመነ ፣ ተካልኝ ደጀኔ
ኤፍሬም አሻሞ ፣ ጋቶች ፓኖም (ሙሉአለም መስፍን) ፣ ሺመልስ በቀለ ፣ ኡመድ ኡኩሪ (አስቻለው ግርማ)
ጌታነህ ከበደ (ባዬ ገዛኸኝ) እና ሳላዲን ሰኢድ(አምበል)
የእለቱ ዳኞች ዘግይተው በመድረሳቸው ጨዋታው ይጀመራል ከተባለበት 9፡30 በ30 ደቂዎች ዘግይቶ 10፡00 ላይ ተጀምሯል፡፡
በጨዋታው የመጀመርያ ደቂቃዎች የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን ተደጋጋሚ ሙከራዎች ማድረግ ችሏል፡፡ በተለይም ሬኒክ ሌኒ ፣ ኔልሰን ሎውረንስ እና አቺሌ ሂኔርቲ አደገኛ ሙከራዎች ማድረግ ችለዋል፡፡
በ23ኛው ደቂቃ በኢትዮጵያ የግብ ክልል ተካልኝ ደጀኔ ኳስ በእጅ በመንካቱ የተሰጠውን ይፍፁም ቅጣት ምት በጨዋታው ጥሩ ሲንቀሳቀስ የነበረው ኔልሰን ሎውረንስ ወደ ግብነት ቀይሮ የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን 1-0 እንዲመራ አስችሎታል፡፡

ከግቡ መቆጠር በኋላ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የተሻለ ለመንቀሳቀስ ቢሞክሩም ያለመረጋጋት እና የውህደት ችግር ታይቶበታል፡፡ የመጀመርያው አጋማሽም በሲሸልስ 1-0 መሪነት ተጠናቋል፡፡
ከእረፍት መልስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከመጀመርያው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረገ ሲሆን በተደጋጋሚ ወደ ግብ መድረስም ችለዋል፡፡ በ2ኛው አጋማሽ የመጀመርያ ደቂቃዎች የሲሸልሱ ትሬቨር ዊዶት በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል፡፡
በ54ኛው ደቂቃ የቀኝ መስመር ተከላካዩ ስዩም ተስፋዬ ኢትዮጵያን አቻ የምታደርግ ግብ በማስቆጠር ዋልያዎቹን ወደ ጨዋታው መልሷቸዋል፡፡ ከግቧ በኋላ ሲሸልሶች ወደ ግብ ክልላቸው ተጠግተው መከላከልን ሲመርጡ ኢትዮጵያ በማጥቃት ወደ ግብ በመቅረብ የግብ እድሎችን ለመፍጠር ጥረት አድርጋለች፡፡ በተለይም በ78ኛው ደቂቃ ሳላዲን ሰኢድ እጅግ ለግብ የቀረበች ኳስ አግኝቶ ሳይጠቀምበት የቀረው የግብ ማግባት እድል የሚቀስ ነበር፡፡
ሲሸልሶች በጨዋታው መገባደጃ ደቂቃዎች ሰአት በማባከን ጨዋታውን በአቻ ውጤት ለመጨረስ የጣሩ ሲሆን ተሳክቶላቸው ጨዋታው 1-1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡
የአቻ ውጤቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በጊዜያዊነት ምድቡን መምራት ጀምሯል፡፡ ኢትዮጵያ ከ2 ጨዋታ 4 ነጥብ ይዛ አንደኛ ደረጃን ስትይዝ ነገ ከሌሶቶ ጋር 2ኛ የምድብ ጨዋታዋን የምታደርገው አልጄርያ በ3 ነጥብ ትከተላለች፡፡ ሲሸልስ በ1 እንዲሁም ሌሶቶ በ0 ነጥብ የዘው ይከተላሉ፡፡
የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን ከ5 ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ነጥብ ተጋርታለች፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን 3ኛ የምድብ ጨዋታውን ከአልጄርያ ብሄራዊ ቡድን ጋር በሜዳው ያደርጋል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating