ፊሊፕ ኦቮኖ በመቐለ ከተማ ውሉን አድሷል
Share
ኤኳቶሪያል ጊኒያዊው ግብ ጠባቂ ፊሊፕ ኦቮኖ በመቐለ ከተማ ለተጨማሪ 1 ዓመት ለመቆየት ተስማምቷል፡፡ ኦቮኖ በመጀመሪያ ዓመት የኢትዮጵያ ቆይታው ስኬታማ ጊዜያትን ከመቐለ ከተማ ጋር አሳልፏል፡፡
ኦቮኖ ወደ ደቡብ አፍሪካ ይመለሳል የሚል ግምት የነበረ ቢሆንም ባልተጠቀሰ ከፍተኛ ደሞዝ በመቐለ ከተማ የነበረውን ውል አድሷል፡፡ ኦቮኖ በቋሚነት በክለቡ አብዛኛውን ጊዜ ያሳለፈ ሲሆን አነስተኛ መጠን ግብ ካስተናገዱ ክለቦች መካከል አንዱ ለሆነው የመቐለ ከተማ ጠንካራ የመከላከል አደረጃጀት ተጨማሪ ጥንካሬን ፈጥሯል፡፡
በኦርላንዶ ፓይሬትስ ተጠባባቂ የነበረው ኦቮኖ በመቐለ ከተማ ያሳየውን ጥሩ እንቅስቃሴ ተከትሎ በግንቦት ወር ሃገሩ ማቻኮስ ላይ ከኬንያ ጋር ባደረገችው የወዳጅነት ጨዋታ ላይ ለብሄራዊ ቡድን መጠራቱ ይታወሳል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት እና ጨዋታዎች ከመቋረጡ በፊት የሚደረጉት የጨዋታ ሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች እንዲህ ተዳሰዋል። አዲስ አበባ ከተማ ከ...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ | 24ኛ ሳምንት ምርጥ 11
እንደ ሁልጊዜው ባሳለፍነው ሳምንት በተደረጉ ጨዋታዎች ላይ ጎልተው የወጡ ተጫዋቾችን ያካተተ ቡድን ሰርተናል። አሰላለፍ (4-3-2-1) ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ -...
ብሔራዊ ቡድኑ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርቧል
የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከቀናት በኋላ ማድረግ የሚጀምረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለተጫዋቾቹ ጥሪ አስተላልፏል። በ2023 በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ...
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል
10:00 ላይ ከናይጄሪያ አቻው ጋር ወሳኝ ጨዋታ የሚጠብቀው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል። በሕንድ ለሚደረገው የሴቶች...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ዓበይት ጉዳዮች (፫) – አሰልጣኞች ትኩረት
በሦስተኛው የሳምንቱ የዓበይት ጉዳይ ፅሁፋችን አሰልጣኞች ላይ ያተኮሩ ሀሳቦች ተዳሰውበታል። 👉 ፋሲል ተካልኝ እና አዳማ ተለያይተዋል በክረምቱ አዳማ ከተማን የተረከበው...
በሦስት ዳኞች ላይ ውሳኔ ተላልፏል
በወላይታ ድቻ እና በኢትዮጵያ ቡና ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ ዳኞች ከፕሪምየር ሊጉ ውድድር ተሸኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ጨዋታ...