ዮሃንስ ሳህሌ የድሬዳዋ ከተማ አሰልጣኝ ሆነዋል
ያለፈውን የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመን በመቐለ ከተማ ያሳለፉት አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ ወደ ድሬዳዋ ከተማ ማምራታቸው ታውቋል፡፡ አሰልጣኙ ስማቸው በከፍተኛ ሁኔታ ከቻምፒዮኑ ጅማ አባ ጅፋር ጋር ተያይዞ ሲነሳ ቢቆይም ምርጫቸው ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያው ክለብ ሆኗል፡፡
ማክሰኞ ጠዋት አሰልጣኝ ዮሃንስ ወደ ጅማ አባ ጅፋር አምርተው ክለቡን ይረከባሉ ተብሎ ቢጠበቅም የሃሳብ ለውጥ ማድረጋቸውን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ ከአሰልጣኙ ጋር ድርድር በማድረግ ቀጥሯቸዋል፡፡ አሰልጣኝ ዩሃንስ በድሬዳዋ ከተማ የ1 ዓመት ውል መፈረማቸውም ታውቋል፡፡
ድሬዳዋ ከተማ የውድድር ዓመቱን በከፍተኛ በጀት ብዙ ተጨዋቾችን አዛውሮ ቢጀምርም የውጤት ቀውስ ውስጥ ገብቶ ላለመውረድ በመታገል ነበር የጨረሰው፡፡ ክለቡ በቀጣዩ አመት ተጠናክሮ ለመምጣት በማሰብ የአሰልጣኝ ለውጥን ምርጫው ያደረገ ሲሆን ቡድኑን በግዜያዊነት ሲመሩት የነበሩት አሰልጣን ስምኦን አባይ ምትክ የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እና መቐለ ከተማ አሰልጣኝ ዮሃንስ ተሹመዋል፡፡
አሰልጣኝ ዮሃንስ አዲስ አዳጊውን ክለብ መቐለ ከተማን አራተኛ ደረጃ ይዞ እንዲያጠናቀቅ ከረዱ በኃላ ውላቸው በመጠናቀቁ ነበር የሰሜን ኢትዮጵያውን ክለብ የለቀቁት፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት እና ጨዋታዎች ከመቋረጡ በፊት የሚደረጉት የጨዋታ ሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች እንዲህ ተዳሰዋል። አዲስ አበባ ከተማ ከ...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ | 24ኛ ሳምንት ምርጥ 11
እንደ ሁልጊዜው ባሳለፍነው ሳምንት በተደረጉ ጨዋታዎች ላይ ጎልተው የወጡ ተጫዋቾችን ያካተተ ቡድን ሰርተናል። አሰላለፍ (4-3-2-1) ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ -...
ብሔራዊ ቡድኑ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርቧል
የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከቀናት በኋላ ማድረግ የሚጀምረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለተጫዋቾቹ ጥሪ አስተላልፏል። በ2023 በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ...
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል
10:00 ላይ ከናይጄሪያ አቻው ጋር ወሳኝ ጨዋታ የሚጠብቀው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል። በሕንድ ለሚደረገው የሴቶች...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ዓበይት ጉዳዮች (፫) – አሰልጣኞች ትኩረት
በሦስተኛው የሳምንቱ የዓበይት ጉዳይ ፅሁፋችን አሰልጣኞች ላይ ያተኮሩ ሀሳቦች ተዳሰውበታል። 👉 ፋሲል ተካልኝ እና አዳማ ተለያይተዋል በክረምቱ አዳማ ከተማን የተረከበው...
በሦስት ዳኞች ላይ ውሳኔ ተላልፏል
በወላይታ ድቻ እና በኢትዮጵያ ቡና ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ ዳኞች ከፕሪምየር ሊጉ ውድድር ተሸኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ጨዋታ...