ደቡብ ፖሊስ የመጀመርያ ተጫዋቹን ሲያስፈርም የሁለት ተጫዋቾችን ውል አድሷል
የከፍተኛ ሊግ የበላይ በመሆን ወደ ፕሪምየር ሊግ ያደገው ደቡብ ፖሊስ በዝውውር መስኮቱ የመጀመርያ ዝውውሩን ማከናወኑን ክለቡ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጿል።
መክብብ ደገፉ ወደ ደቡብ ፖሊስ ያመራ ተጫዋች ነው። ግብ ጠባቂው መክብብ የውድድር ዓመቱን በሀምበሪቾ ያሳለፈ ሲሆን በ2006 ከወላይታ ድቻ ጋር ወደ ፕሪምየር ሊግ በማደግ በተለይ የመጀመርያው ዓመት ላይ ጥሩ ጊዜ ማሳለፍ ችሎ ነበር። መክብብ ከወላይታ ድቻ ከለቀቀ በኋላ በሀዋሳ ከተማ እና አዳማ ከተማ ያልተሳኩ ጊዜያትን ካሳለፈ በኋላ ነበር ወደ ሀምበሪቾ ያመራው። ደቡብ ፖሊስ መክብብን በአንድ ዓመት ውል ያስፈረመው ሲሆን ወደ ወላይታ ድቻ ያመራው መኳንንት አሸናፊን ክፍተት እንደሚሸፍን ታምኖበታል።
ደቡብ ፖሊስ የሁለት ተጫዋቾችንም ውል አድሷል። ክለቡ ወደ ፕሪምየር ሊግ እንዲያድግ ከረዱ ተጫዋቾች መካከል የሚጠቀሱት ብርሀኑ በቀለ እና ሙህዲን ዐብደላ ውላቸው ለተጨማሪ አንድ ዓመት የታደሰላቸው ተጫዋቾች ናቸው።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...