የአስቻለው ግርማ ማረፍያ ሀዋሳ ከነማ ሆኗል
የ2007 የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ተፋላሚው ሀዋሳ ከነማ የኢትዮጵያ ቡናው የመስመር አጥቂ አስቻለው ግርማን የግሉ አድርጓል፡፡
ከኢዮጵያ ቡና ጋር የነበረው ውል ከተጠናቀቀ በኋላ ስሙ በተለይም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ሲያያዝ የከረመው አስቻለው በመጨረሻም ለአንድ አመት ለደቡቡ ክለብ ለመጫወት ከስምምነት ላይ ደርሷል፡፡ ወርሃዊ 62ሺህ ብር ይከፈለዋልም ተብሏል፡፡
የሀዋሳ ከነማው አሰልጣኝ በዝውውሩ ዙርያ ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት አስቻለው ለክለቡ ለመጫወት ተስማምቷል፡፡ ‹‹ ባለኝ መረጃ መሰረትበቃል ደረጃ ተስማምተናል፡፡ ዛሬ ፊርማውን ያኖራል፡፡ በፌዴሬሽን ተገኝቶ በይፋ ሲፈራረም ነው ሁሉንም ነገር መናገር የምንችለው›› ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል
በባሌ ከተማ የተወለደው አስቻለው ግርማ በ2005 አጋማሽ ከሱሉልታ ከነማ ወደ ኢትዮጵያ ቡና ከተሸጋገረ በኋላ በየአመቱ ከፍተኛ መሻሻል በማሳየት በሀገሪቱ ከሚጠቀሱ ምርጥ የመስመር አጥቂዎች ተርታ ለመሰለፍ በቅቷል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎች – ኑራ ኢማም
ተዛማጅ ፅሁፎች
ሀዲያ ሆሳዕና የዕግድ ውሳኔ ተላለፈበት
ሀዲያ ሆሳዕና ከዚህ ቀደም በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተሰጠበትን ውሳኔ ተግባራዊ አላደረገም በሚል የዕግድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ለ15 ተጫዋቾች...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | መከላከያ 1-2 ሀዋሳ ከተማ
ሀዋሳ ከተማ ከመመራት ተነስቶ በማሸነፍ በሦስተኛነት ፉክክሩ ከቀጠለበት ጨዋታ በኋላ ተጋጣሚ አሰልጣኞች ይህንን ብለዋል። አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ - መከላከያ ስለሁለቱ...
ሪፖርት | ሀዋሳ ከተማ መከላከያን አሸንፏል
ሀዋሳ ከተማዎች ደካማ በነበሩበት ጨዋታ አስፈላጊውን ሦስት ነጥብ ከመከላከያ መንጠቅ ችለዋል። መከላከያዎች በመጨረሻው የጨዋታ ሳምንት ከአዳማ ጋር ያለግብ አቻ ከተለያየው...