ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ውይይት ሊያደርግ ነው
ኢትዮጵያ ቡና በትኬት ሽያጭ ገቢ ላቀረበው ጥያቄ ፌዴሬሽኑ ምላሽ ለመስጠት ቀጠሮ ይዟል።
ኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የ2010 የአዲስ አበባ ስታድየም ገቢ ድርሻ እንዲሰጠው እና የዘንድሮው የውድድር ዘመን የስታድየም ትኬት ሽያጭ በክለቡ አማካኝነት እንዲከናወን ፤ ይህ በአስቸኳይ ካልተፈጸመም ውድድር እንደማያደርግ የሚገልጽ ደብዳቤ ለፌዴሬሽኑ ማስገባቱን በዛሬው ዕለት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
ደብዳቤውን የተመለከተው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንም በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ ለመስጠት ‹‹ነገ 10:00 ተገናኝተን እንወያይ›› ሲል ለኢትዮዽያ ቡና የቦርድ አመራሮች ቀጠሮ ሰጥቷል።
በኢትዮጵያ ቡና በኩል የቦርድ ሰብሳቢው መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ ፣ ም/ል ሰብሳቢ አቶ ይስማሸዋ ሥዩም እና የደጋፊ ማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ ክፍሌ አማረ ክለቡን በመወከል ከፌዴሬሽኑ ጋር ውይይት ለማድረግ በተያዘው ቀጠሮ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ ችለናል።
ኢትዮጵያ ቡና በዚህ ጉዳይ በቀዳሚነት ቅሬታውን በይፋ ይግለጽ ያንሳ እንጂ በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎች ክለቦችም ጥያቄ እንዳላቸው በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ ፌዴሬሽኑም ባለፉት ዓመታት የተፈጠሩ መሰል ስህተቶችን ዘንድሮ ላለመስራት ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን በፕሪምየር ሊግ ዓመታዊ ስብሰባ ወቅት መግለፁ ይታወሳል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ24ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
የ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ነገ ሲጀምሩ በዕለቱ የሚደረጉ ሁለት ፍልሚያዎችን እንደሚከተለው ዳሰናቸዋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ ቡና የደረጃ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...