ፌዴሬሽኑ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎችን ያለ ፍቃድ በቀጥታ እንዳይተላለፉ አስጠነቀቀ
የኢትዮጵያ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታን በቀጥታ ስርጭት ማስተላለፍን አስመልክቶ የፌዴሬሽኑ መተዳደርያ ደንብን መሠረት ባደረገ መልኩ እንዲሆን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ለክለቦች በላከው ደብዳቤ አሳሰበ።
በአዲስ መልክ መካሄድ ከጀመረ 21ኛ ዓመቱን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2011 የውድድር ዘመን ሊጀመር ዋዜማ ላይ በምንገኝበት ወቅት ሚዲያዎች ጨዋታዎችን ከፌዴሬሽኑ ፈቃድ ውጭ ማስተላለፍ እንደማይቻል በደብዳቤ ትዕዛዝ አስተላልፏል። ፌዴሬሽኑ ከ2010 ጀምሮ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎችን መገናኛ ብዙሀንን በመጠቀም በቀጥታ ስርጭት ማስተላለፍ የማይቻል መሆኑን ከዚህ ቀደም መግለፁን አስታውሶ በደብዳቤው “በ2011 ማንኛውም ውድድር በሚከናወንበት ወቅት በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን መተዳደርያ ደንብ አንቀፅ 51 መሠረት ፈቃድ ያላገኘ ተቋም ማስተላለፍ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እያሳወቅን ደንቡን የማስከበር ኃላፊነት የሁሉም ባለድርሻ አካል መሆኑን በቅድሚያ እናሳውቃለን” ብሏል።
የደብዳቤ ዝርዝር ፍሬ ኃሳብ አስመልክቶ የፌዴሬሽኑ የፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ገብረሦላሴ በሰጡት አስተያየት ህዝቡ መረጃ ማግኘት እንዳለበት ፌዴሬሽኑ ቢያምንም የውድድሩን የሚመራው ፌዴሬሽኑ በመሆኑ በቀጥታ ስርጭት የሚያስተላልፈው መገናኛ ብዙሀን ከስፖንሰር ከሚያገኘው ገቢ ፌዴሬሽኑ ተጠቃሚ መሆን ስለሚገባው ውድድሮችን ለማስተላለፍ የሚፈልግ ማንኛውም አካል ከፌዴሬሽኑ ጋር በመነጋገር ፈቃድ ሲያገኝ ማስተላለፍ እንደሚችል ገልፀዋል።
ግልፅ የሆነ የብሮድካስቲንግ ህግ እና የፍቃድ መስፈርቶች በሌሉት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከላይ ከተጠቀሰው ደንብ በተቃራኒው በ2010 የውድድር ዓመት በርካታ ጨዋታዎች የቴሌቪዥን እና ራዲዮ የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ማግኘታቸው የሚታወስ ነው።
ማስታወቂያ |
የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የዋናው እግርኳስ ቡድን የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች የቪድዮ ቀረጻ እና የጨዋታ ትንተና የሚያደርግ ባለሙያ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በዚህ ሙያ ላይ የተሰማሩ አካላት በስራው ላይ ያላቸውን የታደሰ ህጋዊ ፍቃድ በመያዝ ሜክሲኮ በሚገኘው የክለቡ ጽህፈት ቤት በአካል በመቅረብ የፍላጎት ማሳወቂያ እና የመወዳደርያ ሰነድ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ – 0115-534949 ; 0115-532051 ኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ |
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ24ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
የ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ነገ ሲጀምሩ በዕለቱ የሚደረጉ ሁለት ፍልሚያዎችን እንደሚከተለው ዳሰናቸዋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ ቡና የደረጃ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...