አስራት አባተ የቢሾፍቱ ከተማ አሰልጣኝ ሆኗል
ባሳለፍነው ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ አሳልፎ የነበረው አስራት አባተ የቢሾፍቱ ከተማ አሰልጣኝ በመሆን ተሹሟል፡፡
በኢትዮጵያ የሴቶች እግር ኳስ ውስጥ ስማቸው በግንባር ቀደሞትነት ከሚጠሩ አሰልጣኞች መካከል አንዱ ነው አሰልጣኝ አስራት አባተ። በተለይ በደደቢት የሴቶች እግር ኳስ ክለብ በነበረው ቆይታ አዳዲስ ተጫዋቾችን በማፍራት እና ክለቡ በሴቶች ፕሪምየር ሊግ ጠንካራ ተፎካካሪ እንዲሆን ማድረግ ችሎ ነበር። የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድንን እየመራም ጠንካራ የማጣሪያ ተሳትፎን እንዳደረገ የሚታወስ ነው።
አሰልጣኙ ከ2009 ጀማሮ የአዲስ አበባ ሴቶች ቡድን አሰልጣኝ በመሆን እስከ ውድድሩ አጋማሽ ከቆየ በኃላ የአሰልጣኝ ስዩም ከበደን መልቀቅ ተከትሎ ወደ ወንዶቹ ቡድን ተዘዋውሮ እስከ አምናው የውድድር ዓመት መጨረሻ ሳምንታት ቆይቷል። አሰልጣኝ አስራት ለጥቂት ጊዜያት ከአሰልኝነት ከራቀ በኃላ ከኢትዮጵያ ቡና ረዳት አሰልጣኝነት እና ከከፍተኛ ሊግ ክለቦች ጋር ስሙ ቢያያዝም የአንደኛ ሊግ ተሳታፊ የሆነውን ቢሾፍቱ ከተማን በአንድ ዓመት የውል ስምምነት በአሰልጣኝነት እንደሚመራ ታውቋል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...