ደደቢት እግርኳስ ክለብ ለፌዴሬሽኑ አቤቱታውን አቀረበ
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት ትግራይ ስታድየም ላይ በደደቢት እና ኢትዮጵያ ቡና መካከል የተካሄደው ጨዋታ “ያለ ክለባችን ፍቃድና እውቅና ውጭ የቀጥታ የሬዲዮ ስርጭት ተካሂዷል።” ሲል ለፌዴሬሽኑ አቤቱታውን አቀረበ።
” የደደቢት እግርኳስ ክለብ ጥቅምት 25 ቀን 2011 ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ባከናወነው ጨዋታ ላይ የአዲስ አበባ መገናኛ ብዙሀን (ኤፍኤም 96, 3) የሬዲዮ ጣቢያ ከእኛም ሆነ ከፌዴሬሽኑ ምንም አይነት ፈቃድና እውቅና ውጭ ጨዋታውን ማስተላለፉ ተገቢ አይደለም። ይህ በመሆኑ ክለቡ በዕለቱ የሜዳ ገቢ ላይ ኪሳራ ያደረሰ ከመሆኑም ባሻገር የህግ ጥሰት ተፈፅሟል።” በማለት በደብዳቤው ገልጾ ፌዴሬሽኑ የተፈፀመውን የህግ ጥሰት እና የደረሰውን ጉዳት ከግምት ውስጥ በማስገባት እርምጃ እንዲወስድ አቤቱታውን አቅርቧል። ደደቢት የመገናኛ ብዙሀን ለሀገራችን እግርኳስ እድገት እያበረከቱት ያለው አስተዋፆኦ ከፍተኛ መሆኑንም አያይዞ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2011 የውድድር ዘመን ጨዋታዎችን ከፌዴሬሽኑ ፈቃድ ውጭ ማስተላለፍ እንደማይቻል በደብዳቤ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ይታወቃል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ24ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
የ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ነገ ሲጀምሩ በዕለቱ የሚደረጉ ሁለት ፍልሚያዎችን እንደሚከተለው ዳሰናቸዋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ ቡና የደረጃ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...