ዳሽን ቢራ የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ላይ ይሳተፋል
በየአመቱ በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት የሚካሄደው የአዲስ አበበ ከተማ ዋንጫ የዘንድሮ ተጋባዥ ክለቦች ጉዳይ እልባት አግኝቷል፡፡ ከአዳማ ከነማ ጋር የሚሳተፈው ሌላኛው የክልል ክለብም ዳሽን ቢራ ሆኗል፡፡
ፌዴሬሽኑ ከዚህ ቀደም እንዲሳተፍ ጥያቄ ያቀረበው ለወላይታ ድቻ ቢሆንም ድቻ ምላሽ ሊሰጥ ባለመቻሉ ግብዣው ወደ ዳሽን ዞሯል፡፡ የጎንደሩ ክለብ በአምናው ውድድር ላይ በተጋባዥነት መካፈሉ የሚታወስ ነው፡፡
የዘንድሮው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ካሌንደር ጋር ተጋጭቷል፡፡ ውድድሩ ይጀመራል የተባለው በመጪው ቅዳሜ ቢሆንም በውድድሩ ላይ ይሳተፋሉ የተባሉት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና መከላከያ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ጨዋታቸውን እሁድ ያደርጋሉ፡፡ ነገ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ የሚጠበቀው ፌዴሬሽኑ የውድድሩ መደራረብ ጉዳይ ላይ ያለው ነገር ባይኖርም ነገ 5፡00 ላይ በወወክማ በሚሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ውድድሩን አስመልክቶ ያሉትን ውዥንብሮች ያጠራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የእጣ ማውጣት ስነስርአቱም አብሮ ይከናወናል፡፡
ፌዴሬሽኑ ወድድሩ ከመስከረም 22 እስከ ጥቅምት 7 እንደሚካሄድ ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...