አርቢቴር ጌቱ ተፈራ ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ
በኢትዮጵያ ኘሪምየር ሊግ የ2ኛ ሳምንት ጎንደር ላይ ፋሲል ከነማ ከሀዋሳ ከተማ የተደረገውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት የመራው ፌዴራል አርቢቴር ጌቱ ተፈራ በጨዋታው የዳኝነት ስህተት ፈፅሟል በሚል የ18 ወራት እገዳ ውሳኔ ተላልፎበታል።
በፋሲል ከነማ 3-1 አሸናፊነት የተጠናቀቀው ጨዋታ በአቻ ውጤት ቀጥሎ ባለበት ሰዓት በ87ኛው ደቂቃ የወሰኑት ውሳኔ ጨዋታውን ለ20 ደቂቃዎች እስከማስተጓጎል ያደረሰ ነበር። ለፋሲል ከነማ የፍፁም ቅጣት ምት በሰጡ ቅጽበት ውሳኔውነረ በመሻር ክስተቱ በፊት የተቆጠረውን ጎል ሲያፀድቁ ኋላ ላይ ደግሞ በድጋሚ ውሳኔያቸውን በመቀየር የፍፁም ቅጣት ምት እንዲመታ አድርገው አዳነ ግርማን ከሀዋሳ በኩል በቀይ ካርድ ማስወጣታቸው ይታወሳል። በዚህ ዙርያ የፌዴሬሽኑ ዳኞች ኮሚቴ ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል።
የፌዴሬሽኑ የቅጣት ውሳኔ ይህንን ይመስላል:-
በኢትዮጵያ ወንዶች ኘሪምየ ር ሊግ የ2011 ዓ.ም የ 2ኛ ሳምን ት ጨዋታ ጥቅምት 25 ቀን 2011 ዓ.ም መርሃ ግብር በጎንደር ስታዲየ ም በፋሲል ከተማና በሐዋሳ ከተማ ክለቦች መካከል በተካሄደ ጨዋታ ላይ የጨዋታው ዋና ዳኛ በነበሩት ፌደራል ዋና ዳኛ ጌቱ ተፈራን አስመልክቶ የጨዋታው ታዛቢ (ኮሚሽነር) ባቀረቡት የአፈጻፀም ሪፖርት እንዲሁም ዋና ዳኛው ጨዋታውን በመሩት ወቅት ስለፈፀሙት የቴክኒክ ስህተት ያቀረቡትን የይቅርታ ደብዳቤ መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ጥቅምት 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በጥልቀትና በስፋት ከተወያየ በኋላ፣
1ኛ. ፌዴራል ዋና ዳኛ ጌቱ ተፈራ የፈፀሙት ከፍተኛ የቴክኒክ ስህተት ከአንድ ሲኒየር ፌዴራል የእግር ኳስ ዳኛ የማይጠበቅ ጥፋት መሆኑን በማስታወስ፣
2ኛ. በፌዴራል ዳኛነት ማገልገል ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ የሚያስቀጣ ስህተት ፈጽመው የማያውቁና ባሳዩት የአፈፃፀም መሻሻል በኤሊት ዳኛነት ውስጥ መግባታቸውን እንዲሁም አስከዚህ ጨዋታ ድረስ የነበራቸውን መልካም አፈፃፀም ከግምት በማስገባት፣
3ኛ. ከጨዋታ ፍጻሜም በኋላ ስለፈፀሙት የቴክኒክ ስህተት በማመንና ለወደፊት ከዚህ ዓይነት ድርጊት ተቆጥበው የሚመደቡበትን ጨዋታ በአግባቡና በትክክል ለመምራት የሚዘጋጁ መሆናቸውን በጽሑፍ በማረጋገጣቸው በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የእግር ኳስ ዳኞች፣ ኢንስትራክተሮችና ታዛቢዎች የሥነ-ስርዓት እርምጃ ደንብ ክፍል 3 አንቀጽ 6 ተራ ቁጥር 6.8.2 እና 6.9 መሠረት ለ1 ዓመት ከ6 ወር ከእግር ኳስ ዳኝነት እንዲታገዱ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ጌቱ ተፈራ ከዚህ ቀደም በ2008 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሊግ ውድድር ላይ የስነ-ምግባር ጥሰት ፈፅሟል በሚል እገዳ ተላልፎበት እንደነበር የሚታወስ ሲሆን በ2010 የውድድር ዘመን ኢትዮጵያ ቡና ከሲዳማ ቡና ያደረጉትን የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ የመራበት መንገድ ከፍተኛ ተቃውሞ አስከትሎ እንደነበር አይዘነጋም፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ24ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
የ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ነገ ሲጀምሩ በዕለቱ የሚደረጉ ሁለት ፍልሚያዎችን እንደሚከተለው ዳሰናቸዋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ ቡና የደረጃ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...