ደቡብ ፖሊስ ሦስት ወጣት ተጫዋቾችን አስፈርሟል
በፌዴሬሽኑ የፎርማት ለውጥ የተነሳ አዲስ ፈርመው ከነበሩ ተጫዋቾች ጋር እንደሚለያይ የሚጠበቀው ደቡብ ፖሊስ ሦስት አዳዲስ ወጣት ተጫዋቾችን ወደ ክለቡ አምጥቷል፡፡
ከቅዱስ ጊዮርጊስ የታዳጊ ቡድኑ የተገኘው ዮሐንስ ዘገየ ወደ ቢጫ ለባሾቹ ቤት ያመራ ተጫዋች ነው፡፡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተስፋ ቡድን ካደገ በኃላ በመጀመሪያው ዓመት ጅማሮ ተስፋ ሰጪ ጊዜን ያሳለፈው ዮሀንስ በሒደት ብዙም መሰለፍ ዕድል ባለማግኘቱ ወደ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ተጉዞ የአንድ ዓመት ቆይታን አድርጎ ነው ወደ ፖሊስ ያመራው፡፡
ይታጀብ ገብረማርያም ሌላኛው አዲስ ፈራሚ ነው፡፡ ከመከላከያ የተስፋ ቡድን የተገኘው ይህ የፊት እና የመስመር አጥቂ ባለፈው ዓመት በአሰልጣኝ ሥዩም ከበደ ወደ ዋናው ቡድን ማደግ ከቻለ በኋላ በክለቡ ጥቂት ጨዋታዎች ላይ ዕድልን ያገኘ ቢሆንም የውል ጊዜ እየቀረው ከመከላከያ ተለያይቶ ፖሊስን ተቀላቅሏል፡፡
እንደ ይታጀብ ሁሉ ከመከላከያ ክለቡን የተቀላቀለው ተጫዋች አብነት ይግለጡ ሆኗል፡፡ ከጦሩ ታዳጊ ቡድን የተገኘውና በዋናው ቡድን ቆይታ የነበረው ይህ ተጫዋች በተከላካይ ስፍራ ላይ ይጫወታል።
በተያያዘ ከደቡብ ፖሊስ ጋር ቅድመ ስምምነት ፈፅሞ የነበረው ዩጋንዳዊው አማካይ ኢቫን ሳካዛ በትላንትናው ዕለት ለአንድ ዓመት ለክለቡ ለመጫወት ፊርማውን አኑሯል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...