አንጋፋው አጥቂ ወደ ቀደሞ ክለቡ ተመልሷል
አንጋፋው አጥቂ ኤሪክ ሙራንዳ በ2010 ቆይታ ላደረገበት ደቡብ ፖሊስ ፈርሟል።
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ለረጅም ዓመታት መጫወት ከቻሉ የውጪ ተጫዋቾች መካከል የሚጠቀሰው ኬኒያዊው አንጋፋ አጥቂ ኤሪክ ሙራንዳ በሀገሩ ኬኒያ እንዲሁም በዓለም ዙርያ ማልዲቭስ፣ ህንድ፣ ቬትናም፣ ሲንጋፖር፣ ማሌዥያ እና ኦማን ክለቦች ውስጥ መጫወት የቻለ ሲሆን በ1995 እና 96 በቅዱስ ጊዮርጊስ ቆይታ ካደረገ በኋላ በድጋሚ በ2006 ተመልሶ ወደ ኢትዮጵያ ከመጣ በኋላ ለሲዳማ ቡና የተጨመወተ ሲሆን በ2010 ደቡብ ፖሊስ፣ ባለፈው ዓመት ደግሞ ሀዲያ ሆሳዕና ጋር ወደ ፕሪምየር ሊግ እንዲያድጉ አስተዋፅኦ አበርክቷል። አጥቂው በተከታታይ ሦስት ዓመታት ወደ ፕሪምየር ሊግ በማደግ ታሪክ ለመስራት ወደ ደቡብ ፖሊስ ተመልሷል።
ኤሪክ ከጋናዊው አዳሙ መሐመድ፣ ከናይጄሪያዊው ላኪ ሰኒ እና ከዩጋንዳዊው ኢቫን ሳካዛ በመቀጠል አራተኛ የክለቡ ውጪ ዜጋ ተጫዋች ሆኗል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...