የአዳማ ከተማ ዋንጫ የዕጣ ማውጣት ሥነ ስርዓት ዛሬ ተደረገ

የአዳማ ከተማ ዋንጫ የዕጣ ማውጣት ስነ-ስርአት ዛሬ በአዳማ ኬኛ ሆቴል በተደረገ ስነስርአት ወጥቷል፡፡

በአዳማ ከተማ ኬኛ ሆቴል በ9:00 በተደረገው ሥነ ስርዓት ስድስት ክለቦች በሁለት ምድብ የተከፈሉ ሲሆን የፊታችን ሀሙስ በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም በሚደረግ የመክፈቻ ጨዋታ የሚጀመር ይሆናል፡፡

ምድብ 1
አዳማ ከተማ፣ ጅማ አባ ጅፋር፣ ሀዲያ ሆሳዕና

ምድብ 2
ፋሲል ከነማ፣ ሀዋሳ ከተማ፣ ድሬዳዋ ከተማ

ሀሙስ ጥቅምት 27 ቀን 2012

08:00 ፋሲል ከነማ ከ ሀዋሳ ከተማ
10:00 አዳማ ከተማ ከ ጅማ አባ ጅፋር

ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን 2012

08:00 አዳማ ከተማ ከ ሀዲያ ሆሳዕና
10:00 ፋሲል ከነማ ከ ድሬዳዋ ከተማ

ሰኞ ኅዳር 1 ቀን 2012

08:00 ሀዲያ ሆሳዕና ከ ጅማ አባ ጅፋር
10:00 ድሬዳዋ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ

ቀጣይ ሳምንት ሀሙስ ከምድባቸው 1ኛ እና 2ኛ የሚወጡ ክለቦች እርስ በእርስ ተጫውተው ለፍፃሜ አላፊ የሚሆኑት ቡድኖች የሚለዩ ይሆናል።


© ሶከር ኢትዮጵያ