የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ሀዲያ ሆሳዕና
ዛሬ በአዳማ ከተማ ዋንጫ ባለሜዳው አዳማ ከተማ በተስፋዬ ነጋሽ እንዲሁም የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው ሀዲያ ሆሳዕና በሄኖክ አርፍጮ ግቦች አቻ ተለያይተዋል። ከጨዋታው በኋላም የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
“ቡድናችን ዛሬ ያሳየው እንቅስቅሴ እየተሻሸለ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።” ደጉ ዱቡሞ
ስለጨዋታው እንቅስቃሴ
“በእንቅስቃሴው ቡድናችን ዛሬ ተስፋ ሰጪ ነገሮችን አድርጓል። ተጋጣሚያችን የሚፈልገውን ነገር እንዳይተግብር በማድረግ እኛ የምንፈልገውን ማድረግ ችለናል። በአጠቃላይ ቡድናችን ዛሬ ያሳየው እንቅስቅሴ እየተሻሸለ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።”
አጋጣሚዎችን ስላለመጠቀም
“ይህ ችግር አሁንም አለ ፤ ይህም ዋጋ አስከፍሎናል። በተቻለን መጠን ጠንክረን ሰርተን ከስር መሰረቱ እንፈታዋለን።”
በቀኝ መስመር ስላደለው የቡድኑ እንቅስቃሴ
“አዎ በቀኝ መስመር አድልተን እያጠቃን በግራውም እንዲሁ ክፍተት ላለመተው ነበር አስበን የገባነው። እንዳያችሁትም ፍልስፍናችን ሰርቶልን ግብ ያስቆጠርነውም ሆነ አብዛኞቹን የግብ ዕድሎች የፈጠርነው ከዛ በሚነሱ ኳሶች ነበር።”
” እንደመጀመሪያ ጨዋታችን እኔ ደስተኛ ነኝ ” ግርማ ታደሰ
ስለቡድኑ እንቅስቃሴ
“ቡድኑ ያያችሁት ነው ፤ ኳስ ለመቆጣጠር ጥረት ያደርጋል። ወደራሱ ሜዳ የሚመጣውን በአግባቡ ይቆጣጠራል። እንደመጀመሪያ ጨዋታችን እኔ ደስተኛ ነኝ ፤ በቀጣይ ከዚህ ተሽለን ብቅ እንላለን።”
ስለማጥቃት እንቅስቃሴው መዳከም
“እውነት ነው ፤ ይህን ችግር እንፈታዋለን። በተለይ በሁለተኛው አጋማሽ መጀመሪያ ላይ ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚቻል ፍንጭ አይተናል። በቀጣይ ይህን እና ሌሎች ችግሮቻችንን ፈትተን ብቅ እንላለን።”
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...