የአሰልጣኞች አስተያየት | ፋሲል ከነማ 2-0 ድሬዳዋ ከተማ
በአዳማ ከተማ ዋንጫ የዛሬ ሁለተኛ ጨዋታ ፋሲል በኦሰይ ማውሊ እና ሙጂብ ቃሲም ግቦች ታግዞ ድሬዳዋን 2-0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ከጨዋታው በኋላም የፋሲል አሰልጣኝ አስተያየታቸውን ሲሰጡ የድሬዳዋውን አሰልጣኝ ስምኦን ዓባይ አስተያየት ማግኘት አልተቻለም።
“በዛሬው የቡድኔ እንቅስቃሴ ደስተኛ ነኝ።” ሥዩም ከበደ
ስለጨዋታው
“ቡድኑ ከወዳጅነት ወዳጅነት ጨዋታ እዚህ ላይ ደርሷል። በዛሬው የቡድኔ እንቅስቃሴ ደስተኛ ነኝ። በተለይም ተጋጣሚያችን ኳስ እንድንጫወት የሚፈቅድ መሆኑ እኛን ጠቅሞናል። ቡድኑ ጥሩ ነው ፤ አሁን ትንሽ ክፍተቶች ብቻ ነው የሚቀረን ይህንንም በቶሎ እናስተካክላለን።”
ስለአጥቂዎቹ ኳስ ማባከን
“ይህ ትልቅ ችግር ነው። በተለይ በመጀመሪያው አጋማሽ ያገኘነውን ንፁህ የሚባሉ የግብ ዕድሎች አባክነናል። እንዲህ ዓይነት ነገር ዋጋ ያስከፍላል ፤ በቀጣይ የሚሻሻል ይሆናል።”
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...