የኢትዮጵያ ዋንጫ ዘንድሮ አይደረግም
የ2012 የኢትዮጵያ ዋንጫ (ጥሎ ማለፍ) ውድድር ዘንድሮ እንዳይደረግ ክለቦች በድምፅ ብልጫ ወሰኑ፡፡
የዘንድሮው የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር እንደማይካሄድ ክለቦች ዛሬ በአዳማ ኤክስኪውቲቭ ሆቴል እየተደረገ ባለው ውይይት ላይ በድምፅ ብልጫ ወስነዋል፡፡ ውድድሩ ክለቦች ለውውድሩ ትኩረት እየሰጡት ባለምጣታቸው እና ለተጨማሪ ወጪ እየዳረጋቸው በመሆኑ የተነሳ ሊሰረዝ ችሏል። በዚህም መሠረት የጥሎ ማለፉን ውድድር በተመለከተ በደንቡ ላይ ሰፍረው የነበሩ አንቀፆች በሙሉ የተሰረዙ ሲሆን በፕሪምየር ሊጉ አንደኛ የሚወጣው ቡድን በቻምፒዮንስ ሊግ ሲሳተፍ የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር በመቅረቱ በሊጉ ሁለተኛ የወጣው ክለብ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የሚሳተፍ ይሆናል፡፡
በአንዳንድ አስገዳጅ ምክንያቶች ሳይካሄዱ ከቀሩባቸው ጥቂት ጊዜያቶች በቀር ከ1937 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ይህ ውድድር ከ2004 በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ የማይደረግ ይሆናል። በወቅቱ ደደቢት ሁለተኛ ደረጃ ይዞ በማጠናቀቅ በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ መሳተፉ ይታወሳል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት እና ጨዋታዎች ከመቋረጡ በፊት የሚደረጉት የጨዋታ ሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች እንዲህ ተዳሰዋል። አዲስ አበባ ከተማ ከ...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ | 24ኛ ሳምንት ምርጥ 11
እንደ ሁልጊዜው ባሳለፍነው ሳምንት በተደረጉ ጨዋታዎች ላይ ጎልተው የወጡ ተጫዋቾችን ያካተተ ቡድን ሰርተናል። አሰላለፍ (4-3-2-1) ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ -...
ብሔራዊ ቡድኑ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርቧል
የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከቀናት በኋላ ማድረግ የሚጀምረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለተጫዋቾቹ ጥሪ አስተላልፏል። በ2023 በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ...
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል
10:00 ላይ ከናይጄሪያ አቻው ጋር ወሳኝ ጨዋታ የሚጠብቀው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል። በሕንድ ለሚደረገው የሴቶች...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ዓበይት ጉዳዮች (፫) – አሰልጣኞች ትኩረት
በሦስተኛው የሳምንቱ የዓበይት ጉዳይ ፅሁፋችን አሰልጣኞች ላይ ያተኮሩ ሀሳቦች ተዳሰውበታል። 👉 ፋሲል ተካልኝ እና አዳማ ተለያይተዋል በክረምቱ አዳማ ከተማን የተረከበው...
በሦስት ዳኞች ላይ ውሳኔ ተላልፏል
በወላይታ ድቻ እና በኢትዮጵያ ቡና ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ ዳኞች ከፕሪምየር ሊጉ ውድድር ተሸኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ጨዋታ...