አዳማ ከተማ ዋንጫ | አዳማ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል
ባለፈው ሳምንት የተጀመረው የአዳማ ከተማ ዋንጫ ዛሬ ሲጠናቀቅ 7:00 ላይ በተደረገው የደረጃ ጨዋታ አዳማ ከተማ በመለያ ፍፁም ቅጣት ምቶች ፋሲልን አሸንፎ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በምድብ እና ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ሲጠቀሙባቸው የነበሩትን በርካታ ተጫዋቾች ለውጠው የገቡ ሲሆን በመጀመርያው የጨዋታ አጋማሽ አዳማ ከተማዎች በተሻለ መንቀሳቀስ የቻሉበት ነበር። በተለይ አጥቂው ሚካኤል ጆርጅ እና ኃይሌ እሸቱ በመስመር በኩል በሚያደርጉት መልካም እንቅስቃሴን ማድረግ ቢችልም ንፁህ የግብ እድሎችን ሲፈጥሩ ግን መመልከት አልቻልንም።
ሚካኤል ጆርጅ በቀኝ በኩል ሰጥቶት ኃይሌ እሸቱ ከግብ ጠባቂው ቴዎድሮስ ጋር ተገናኝቶ ብረት የመለሰበት እና ከቅጣት ምት ሚካኤል ጆርጅ ያገኛት እና ወደ ግብ መትቶ የተመለሰበት ተጠቃሽ ሁለት ሙከራዎች ሲሆኑ በአንፃሩ ዐፄዎቹ ከማጥቃት ይልቅ አጋማሹን በኳስ ንክኪ ብቻ የተገደበ አጨዋወትን ተከትለዋል፡፡
በሁለተኛው አጋማሽ በርካታ የኳስ መንሸራሸሮችን በሜዳ ላይ ሁለቱም ቡድኖች ቢያሳዩንም ኢዙ አዙካ በፋሲል በኩል ከቅጣት ምት መቶ ለጥቂት የወጣችበት እና ሚካኤል ጆርጅ ነፃ አቋቋም ላይ ለሚገኘው ተስፋዬ ነጋሽ ሰጥቶት ተስፋዬ ያመከናት ኳስ በጉልህ ሊጠቀሱ የሚችሉ ሁለት የአጋማሹ ሙከራዎች ናቸው።
ፋሲል ከነማዎች በተለይ ሙጂብ ቃሲምን ቀይረው ካስገቡ በኃላ ተጨማሪ ዕድሎቸን ለመፍጠር ጥረቶችን ማድረግ የቻሉ ቢሆንም መደበኛው ክፍለ ጊዜ ያለግብ 0-0 በመጠናቀቁ በተሰጠው የመለያ ምት የፋሲሎቹ አምሳሉ ጥላሁን እና እንየው ካሳሁን የመለያ ሲያመክኑ በአዳማ በኩል ቴዎድሮስ በቀለ ብቻ በመሳቱ አዳማ ከተማ 4-2 አሸንፎ ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ የነሀስ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...