የአሰልጣኞች አስተያየት | ሀዲያ ሆሳዕና 0-1 ሀዋሳ ከተማ
3ኛው የአዳማ ከተማ ዋንጫ ዛሬ ፍፃሜውን ሲያገኝ ሀዋሳ ከተማ ተጋጣሚው ሀዲያ ሆሳዕናን 1-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ቻምፒዮን ሆኗል። ከጨዋታው በኋላም የሁለቱ ቡድን አሰልጣኞች ስለጨዋታው እና በውድድሩ ላይ ስለነበራቸው ቆይታ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
” በጨዋታዎቹ ላይ ለማየት የምፈልገውን ነገር አይቻለው” አዲሴ ካሴ
ስለጨዋታው እንቅስቃሴ
ተጫዋቾቼ በየጨዋታው የነበራቸው የማሸነፍ ፍላጎት ስኬታማ አድርጎናል። ተጋጣሚያችን ሀዲያ ሆሳዕና እጅጉን ጠንካራ ቡድን ነው። ሆኖም ተጫዋቾቼ የሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ተወጥተዋል። በተጨማሪም ሆሳዕና ከፋሲል ሲጫወት በደንብ አይተነው ነበር። ቡድናችንን በዛ መልክ ነው ያዘጋጀነው። የተጫዋቾቼ የማሸነፍ ፍላጎትም ስኬታማ አድርጎናል።
ስለ ውድድሩ ቆይታቸው
የአዳማ ውድድር ለኛ በጣም ነው የረዳን። ቡድናችን ልምምዱን ሲያደርግ የነበረው በሰው ሰራሽ ሜዳ ላይ ነበር። በተፈጥሮ ሳር ላይ ቡድኑ ምን ይመስላል የሚለውን እየተመለከትን፤ ከጨዋታ ጨዋዎፀታ እያሻሻልን እዚህ ደርሰናል። አሁን ይበልጥ ባየነባቸው ክፍተቶች ሰርተን ወደ ፕሪምየር ሊጉ ብቅ እንላለን።
” ውድድሩ ከወዲሁ ድክመት እና ጥንካሬያችንን እንድናውቅ ረድቶናል” ግርማ ታደሰ
ስለጨዋታው እንቅስቃሴ
ዛሬ ካደረግናቸው ጨዋታዎች ሁሉ እጅጉን የተሻለ ነበር። በአዳማው ውድድር ቡድኑ ከዕለት ወደ ዕለት እየተሻሻለ ነው የመጣው። ዛሬ እስካሁን ካደረግናቸው ጨዋታዎች ሁሉ እጅጉን የተሻልን ነበርን። ተጋጣሚያችን በቀላሉ ጎል እንዳይቆጥርበት በራሳቸው የሜዳ ክፍል በቁጥር እጅግ በዝተው መጫወት መቻላቸው ያገኙትን የግብ እድል ደግሞ የኛም ስህተት ታክሎበት አስቆጠሩ እንጂ በእንቅስቃሴም ሆነ በርካታ የግብ ዕድል በመፍጠር የተሻለ ነበርን።
ስለ ቆይታቸው
በአዳማ ቆይታዬ ፕሪምየር ሊጉ ምን ይመስላል የሚለውን አይቼበታለው። በሙሉ ተሳታፊ ቡድኖች በፕሪምየር ሊጉ ብዙ ቆይታ ያላቸው ናቸው። ከዛ አንፃር ፕሪምየር ሊጉ ውስጥ ተፎካካሪ መሆን የሚችል ቡድን ነው። የሲቲ ካፑ መኖር ክፍተታችንን እንዲሁም ጥንካሬያችንን ለይቸበታለሁ።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...