የአንደኛ ሊግ የ2012 ውድድር የእጣ ማውጣት ሥነ-ስርዓት ተካሄደ
በዛሬው ዕለት በራስ ሆቴል በተካሄደው መርሃግብር የ2011 የውድድር ዘመን ግምገማና በመጪው ታህሳስ 5 የሚጀምረው የአዲሱ የውድድር ዘመን የእጣ ማውጣት ሥነ-ስርዓት ተካሂዷል።
መርሐግብሩን በክብር እንግድነት በመገኘት በንግግር ያስጀመሩት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ዘሪሁን ቀቀቦ ውድድሩ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ አደራ አዘል መልዕክት አስተላፈዋል።
በመቀጠልም ተሳታፊ ከሆኑት 60 ክለቦች መካከል 41 ክለቦች መገኘታቸው በመረጋገጡ መርሐግብሩ እንዲቀጥል ተደርጓል።
በመቀጠልም የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ፀሀፊ በሆኑት አቶ አላዩ አማካነት የ2011 የውድድር አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቧል። በሪፖርቱ በርካታ የተለመዱ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን በተለይም በክለቦች በኩል የሚስተዋለው የኢሜይል አጠቃቀም አናሳ መሆኑ እንደ ተግዳሮት በስፋት ተነስቷል።
በመቀጠል በቀረበው ሪፖርትና ስለ አዲሱ የውድድር ዘመን ደንብ ዙሪያ ላይ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብ አስተያየቶች ተሰጥተዋል። ከዓመታዊ ክፍያ፣ ምድብ አደላደልና መርሃግብር አወጣጥ እንዲሁም ከሊጉ ስያሜና የሚዲያ ሽፋን ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ ሀሳቦች ተነስተዋል። በተጨማሪም በሊግ ኮሚቴው በቀረበው የማጠቃለያ ውድድርን በማስቀረት ከየምድቡ አንደኛ የወጡ ቡድኖች በቀጥታ ወደ ከፍተኛ ሊግ እንዲያድግ በቀረበው ሀሳብ ዙርያ በርካታ ሀሳቦች ሀሳቦች በሁለቱም ፅንፍ ተነስተዋል።
በማስከተል በተነሱት ጉዳዮች ላይ የሚመለከታቸው የፌደሬሽኑ እንዲሁም የሊጉ የበላይ ሀላፊዎች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል። በዚህም ውድድሩ ህየኅዳር 28 ይጀመራል ቢባልም የውድድሩ ጅማሮ ከፌዴሬሽኑ ጠቅላላ ጉባኤየዔ ጋር ቀኑ በመገጣጠሙ የውድድሩ ጅማሮ ወደ ታህሳስ 5 ስለመቀየሩ ማረጋገጫ ተሰጥቷል። ተያይዞም የማጠቃለያ ውድድሩ እንደሚቀጥል ተጠቅሷል።
በስተመጨረሻ በሊግ ኮሚቴው ከዚህ ቀደም ከነበረው የምድብ ድልድል የተለየ ወጪ ቁጣቢ የሆነና ክለቦችን በቅርብ ካሉ አጎራባች ክለቦች ጋር የቀረበው አማራጭ ሀሳብ በአዲስአበባ ክለብ ተወካዮች ዘንድ ከአጠቃላይ የስፖርቱ መርህና በክልሎች መካከል ያለውን አብሮነት ላይ ተፅዕኖ ይፈጥራል ተብሎ በቀረበው ተቃውሞ ድልድሉ ከዚህ ቀደም በነበረው መልኩ እንዲቀጥል ተወስኗል። ለአዲሱ አማራጭ የድልድል ሀሳብ ተግባራዊ መደረግ አፅንኦት ሰጥተው ሲከራከሩ የነበሩት የትግራይ ክልል ተወካይ ክለቦችም ውሳኔውን በመቃወም የዕጣ ማውጣት ሥነ-ስርአቱን ረግጠው ወጥተዋል።
የውድድሩ ምድብ ድልድል ይህንን ይመስላል
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...