“ወደ ስሑል ሽረ ለመምጣት የወሰንኩት በዋነኝነት ከብሔራዊ ቡድኑ ላለመራቅ ነው” ምንተስኖት አሎ
በተከታታይ አራት ጨዋታዎች ግቡን ያላስደፈረው ምንተስኖት አሎ ስለ ወቅታዊ አቋሙ ይናገራል።
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ወደ እግሩ ኳሱ ብቅ ካሉት ተስፈኛ ግብ ጠባቂዎች አንዱ ነው። በሰበታ ከተማ፣ ፋሲል ከነማ እና ባህር ዳር ከተማ መጫወት የቻለው ምንተስኖት አሎ በተለይም ባህር ዳር ከተማ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ሲያድግ ጉልህ ድርሻ ነበረው።
ባለፈው ዓመት በዋናው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን መጫወት የጀመረው ይህ ግብ ጠባቂ በዚህ ዓመት ወደ ስሑል ሽረ ተዘዋውሮ ጥሩ ብቃት በማሳየት ይገኛል። በመጀመርያዎቹ ጨዋታዎች ጥሩ ብቃቱን ለማውጣት ተቸግሮ የነበረው ምንተስኖት አሎ ባለፉት አራት ጨዋታዎች ወደ ጥሩ ብቃቱ ተመልሶ በአራት ተከታታይ ጨዋታዎች ግቡን ሳያስደፍር መውጣት ችሏል።
ተጫዋቹ ስለ ወቅታዊ ብቃቱ፣ ስለ ቀጣይ እቅዱ እና ተያያዥ ጉዳዮች ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል።
👉 ስለ ወቅታዊ አቋሙ
ቡድናችን አዲስ ነው። ማለቴ በዚህ ዓመት ነው የተዋቀረው። በበርካታ አዳዲስ እና ወጣት ተጫዋቾች የተገነባ ቡድን ነው ያለን። በዚህም መጀመርያ አከባቢ ትንሽ መንገራገጮች ነበሩ። ከዛ በኃላ ብዙ ግን መሻሻሎች አሳይተናል። የሚሰጠኝን ልምምድ በአግባቡ እየተከታተልኩ በጥሩ ብቃት ላይ እገኛለው። ከዚህ ባለፈም ቡድናችን በመጀመርያዎቹ ጨዋታዎች የነበሩበትን የመከላከል ክፍተቶች ለማሻሻል ከቡድን ጓደኞቼ ጋር ጠንክረን በመስራት ለተከታታይ አራት ጨዋታዎች ግባችንን አላስደፈርንም። በግሌም ግቦችን እንዳይቆጠሩ በመከላከል እና የቡድን ጓደኞቼን ከኋላ ሆኜ በመምራት የበኩሌን እየተወጣው እገኛለው።
👉 በተከታታይ ጨዋታዎች ግቡ አለማስደፈሩ የፈጠረለት ስሜት
ይህ ነገር እንደ ቡድን ነው ያሳካነው ሁሉም የቡድናችን አባል ጠንክሮ በመስራቱ የመጣ መሻሻል ነው። በግሌ ግን በጣም ደስ ብሎኛል። በቀጣይም ከዚህ የተሻለ ነገር እንድሰራ ጥሩ መነሳሻ ነው ሚሆነኝ።
👉 ቡድኑ ስላሳየው መሻሻል
አዎ በውድድሩ መጀመርያ ችግሮች ነበሩ። እንደ ቡድንም በግልም። ቅድም እንዳልኩት ቡድናችን አዲስ የተዋቀረ ቡድን እንደመሆኑና በቅድመ ውድድር ላይ በቂ የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች አለማድረጉ ክፍተቶች ፈጥሮብናል። በሒደት ግን አሰልጣኞቻችን በሰሩት ሥራ ቡድናችን ተዋህዶ አሁን በጥሩ ብቃት ላይ ይገኛል።
👉 ስለ ቀጣይ እቅዱ
ወደ ስሑል ሽረ ለመምጣት የወሰንኩት በዋነኝነት ከብሔራዊ ቡድኑ ላለመራቅ ነው። በጥቅማ ጥቅም ደረጃ የተሻሉ ጥያቄዎች ቀርበውልኝ ነበር። ሆኖም የመጫወት ፍላጎት ስላለኝ እና ከብሄራዊ ቡድን ላለመራቅ የተሻሉ ነገሮች ትቼ ነው ወደ ሽረ የመጣሁት። በቀጣይም ከፈጣሪ ጋር ክለቤም ከብሄራዊ ቡድኔም በተሻለ ብቃት ለማገልገል ጠንክሬ እሰራለው።
በሊጋችን የውጭ ሀገር ተጫዋቾች ይበዛሉ። ይህም በሀገር በቀለ ግብ ጠባቂዎች እድገት ላይ ጥሩ ያልሆነ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ24ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
የ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ነገ ሲጀምሩ በዕለቱ የሚደረጉ ሁለት ፍልሚያዎችን እንደሚከተለው ዳሰናቸዋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ ቡና የደረጃ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...