ስሙ ከበርካታ ክለቦች ጋር ሲያያዝ የነበረው ባዬ ገዛኸኝ በወላይታ ድቻ ለመቆየት ተስማማ

በዝውውር ገበያው እምብዛም እየተሳተፉ የማይገኙት የጦና ንቦቹ የወሳኝ ተጫዋቻቸውን ውል ለማደስ ተስማምተዋል።

በአሰልጣኝ ደለለኝ ደቻሳ የሚመሩት ወላይታ ድቻዎች 4 ወጣት ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸው ለመቀላቀል መስማማታቸው ይታወሳል። ከዚህ ጎን ለጎንም ቡድኑ የነባር ተጫዋቾችን ውል እያደሰ ይገኛል። ከደቂቃዎች በፊት ደግሞ ፈጣኑ አጥቂ ባዬ ገዛኸኝ ከቡድኑ ጋር ለቀጣይ 2 ዓመታት ለመቆየት ፊርማውን አኑሯል።

ለስልጤ ወራቤ፣ ወላይታ ድቻ፣ መከላከያ እንዲሁም ሲዳማ ቡና ጥሩ ግልጋሎት የሰጠው ይህ ተጫዋች በተሰረዘው የውድድር ዘመን ዳግም ወደ ወላይታ ድቻ አምርቶ ሲጫወት ታይቷል። ሊጉ እስከሚቋረጥ ድረስም 9 ግቦችን አስቆጥሮ 1 ግብ የሆነ ኳስ ለቡድን አጋሩ አመቻችቶ ማቀበሉ ይታወሳል።

© ሶከር ኢትዮጵያ


👉እጅዎን በተደጋጋሚ በሳሙና በአግባቡ በመታጠብ አልያም አልኮል እና ሳኒታይዘር በመጠቀም

👉ከሰዎች ጋር ንክኪ በማስወገድ

👉ከአላስፈላጊ እንቅስቃሴ በመገደብ፣ አካላዊ ርቀት በመጠበቅ እና በቤት በመቆየት ራሳችንን ከኮሮና ቫይረስ እንጠብቅ!