ክለቦች የቅድመ ውድድር ዝግጅት ማከናወን ሊጀምሩ ነው
ለ2013 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመን ክለቦች የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን ሊጀምሩ ተሰናድተዋል፡፡
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወደ ሀገራችን ከገባ ጊዜ አንስቶ በሀገራችን ሲደረጉ የነበሩ እግር ኳሳዊ ውድድሮች ሙሉ በሙሉ በመጋቢት ወር አጋማሽ 2012 ጀምሮ መሰረዛቸው ይታወቃል፡፡ ከስድስት ወራት በላይ ተዘግቶ የቆየው ውድድር በድጋሚ በቅርቡ እንደሚመለስ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳይያስ ጅራ በዛሬው ዕለት ለኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ክለቦች ማብሰራቸው የሚታወቅ ሲሆን ክለቦችም ለ2013 የፕሪምየር ሊግ ውድድር ይረዳቸው ዘንድ በቅርብ ቀናት ወደ ቅድመ ውድድር ዝግጅት ሊገቡ እቅድ መያዛቸውን ሶከር ኢትዮጵያ ያገኘችው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ስድስት የሚሆኑ የሊጉ ክለቦችም ከመስከረም 20 በኃላ ባሉ ቀናት ዝግጅት ለማድረግ እንደሚገቡ ሰምተናል፡፡
የሊግ ኩባንያው ምናልባትም ነገ የፕሪምየር ሊጉን ማስጀመሪያ ቀን ይፋ የሚያደርግ ከሆነ ክለቦች ወደ ዝግጅት ሲገቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ሊከተሉ እንደሚገባ መመሪያ እንደሚሰጣቸው ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
👉እጅዎን በተደጋጋሚ በሳሙና በአግባቡ በመታጠብ አልያም አልኮል እና ሳኒታይዘር በመጠቀም
👉ከሰዎች ጋር ንክኪ በማስወገድ
👉ከአላስፈላጊ እንቅስቃሴ በመገደብ፣ አካላዊ ርቀት በመጠበቅ እና በቤት በመቆየት ራሳችንን ከኮሮና ቫይረስ እንጠብቅ!
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...