አትዮጵያዊያን ዳኞች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያን ይመራሉ
ሞሮኒ ላይ ኮሞሮስ ኬንያን የምታስተናግድበት የአፍሪካ ዋንጫ አራተኛ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታን ኢትዮጵያዊያን ዳኞች እንዲመሩ በካፍ ተመድበዋል፡፡
በምድብ ሰባት ኮሞሮስ ኅዳር 6 ኬንያን በሞሮኒ በሚገኘው ስታድ ሞሮኒ ማሎዚኒ ስታዲየም ላይ ስታስተናግድ በዓምላክ ተሰማ በመሐል ዳኝነት ይመራዋል፡፡ ለረጅም ዓመታት በወጥነት በርካታ ጨዋታዎችን የመራው በዓምላክ ባለፈው ሳምንት በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ የግብፁ ፒራሚድ እና ሆሮያን ጨዋታ እንደመራ ይታወሳል፡፡
በረዳት ዳኝነት ከበዓምላክ ጋር የተመደቡት ክንዴ ሙሴ እና ተመስገን ሳሙኤል ሲሆኑ አራተኛ ዳኛ በመሆን የሚያገለግለው ደግሞ ለሚ ንጉሴ መሆኑ ታውቋል፡፡ ይህን ጨዋታ የሲሼልስ ዜግነት ያላቸው ሲሞን ፊልፕ በኮሚሽነርነት ይመሩታል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
👉ሳንዘናጋ አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ራሳችንን ከኮሮና ቫይረስ እንጠብቅ!
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...