ወላይታ ድቻ ከ አዳማ ከተማ : ቀጥታ የፅሁፍ ስርጭት

ወላይታ ድቻ 2-0 አዳማ ከተማ

24′ መሳይ አንጪሶ

85′ ዮሴፍ ዴንጌቶ


 

ተጠናቀቀ!!!

ጨዋታው በወላይታ ድቻ 2-0 አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡ አዳማ ከተማ የውድድር ዘመኑን 2ኛ ሽንፈት አስተናግዶ ሊጉን የመምራት እድሉን አምክኗል፡፡ ወላይታ ድቻ ደግሞ ወደ 6ኛ ደረጃ ከፍ ብሏል፡፡

 

90′ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ 4ኛ ዳኛው ተጨማሪ 4 ደቂቃ አሳይተዋል፡፡

index90′ የተጫዋች ለውጥ ወላይታ ድቻ

ስንታየሁ መንግስቱ ገብቶ አላዛር ፋሲካ ወጥቷል

cb5a1f78247d0a65650169ebbe0e77af8c619332e59a7b232c7d6476799611fb_ originalጎልልል!!! ወላይታ ድቻ

85′ ዮሴፍ ዴንጌቶ በአንድ ሁለት ቅብብል ያገኘውን ኳስ መሬት ለመሬት መትቶ የድቻን 2ኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡

 

index80′ የተጫዋች ለውጥ

አዳማ ከተማ ቡልቻ ሹራ ገብቶ እሸቱ መና ወጥቷል

ወላይታ ድቻ ተክሉ ታፈሰ ገብቶ ሙባረክ ሽኩሪ ወጥቷል

77′ የቀድሞ ክለቡን በአዳማ ማልያ ለመጀመርያ ጊዜ እየገጠመ የሚገኘው እሸቱ መና ከማዕዘን ምት የተሻማውን ኳስ ሞክሮ ጃኮብ ይዞበታል፡፡

67′ ወደ አዳማ የግብ ክልል በረጅሙ የተላከውን ኳስ በግብ ጠባቂው ጃኮብ ስህተት ወደ ጥሩ የግብ ማግባት አጋጣሚነት ቢቀየርም አላዛር ሳጠቀምበት ቀርቷል፡፡ አሰልጣን መሳይ ተፈሪ የድቻ ደጋፊዎች ቡድናቸውን እንዲያበረታቱ በማነሳሳት ላይ ይገኛል፡፡

index65′ የተጫዋች ለውጥ

አዳማ ከተማ ዮናታን ከበደ ወጥቶ ጫላ ድሪባ ገብቷል

ወላይታ ድቻ ፀጋዬ ብርሃኑ ወጥቶ ፀጋ አለማየሁ ገብቷል

soccer-referees-hand-with-red-card-soccer-referees-hand-with-red-card_83761249ቀይ ካርድ

63′ ሚካኤል ጆርጅ በዮሴፍ ዴንጌቶ ላይ ከባድ ፋውል ሰርቷል በሚል በቀጥታ የቀይ ካርድ ተመልክቷል፡፡ አሁን ከሁለቱም አንድ አንድ ተጫዋች ወጥቷል፡፡

soccer-referees-hand-with-red-card-soccer-referees-hand-with-red-card_83761249ቀይ ካርድ

52′ ግቡን ያስቆጠረው መሳይ አንጪሶ በማዕዘን ምት ሽሚያ ወቅት ጥፋት ሰርተሃል በሚል በሁለተኛ ቢጫ ከሜዳ ተወግዷል፡፡ ወላይታ ድቻዎች ውሳኔውን ባለመቀበል ክስ አስመዝግበዋል፡፡ ጨዋታው አሁን ውጥረት እየነገሰበት ይገኛል፡፡

51′ አዳማዎች በተከታታይ 4ኛ የማእዘን ምታቸውን አግኝተዋል፡፡ ቀይ ለባሾቹ የአቻነት ጎል ለማግኘት ጫና በመፍጠር ላይ ይገኛሉ፡፡

47′ ከማዕዘን ምት የተሻማውን ኳስ ዮናታን ከበደ በግንባሩ ገጭቶ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቶበታል፡፡ አስደንጋጭ የግብ ሙከራ ነበር፡፡

whistle-51245′ ሁለተኛው አጋማሽ ተጀመረ

 

indexየተጫዋች ለውጥ: አዳማ ከተማ

ደሳለኝ ደባሽ ገብቶ ፋሲካ አስፋው ወጥቷል፡፡

 


 

የመጀመርያው አጋማሽ ተጠናቀቀ

ወላይታ ድቻ በግሩም ደጋፊ እና በመሳይ አንጪሶ ጎል ታግዘው የመጀመርያውን አጋማሽ 1-0 እየመሩ እረፍት ወጥተዋል፡፡

45′ የመጀመረያው አጋማሽ መደበኛ ደቂቃ ተጠናቆ 4ኛው ዳኛ ተጨማሪ 4 ደቂቃ አሳይተዋል፡፡

30′ አዳማ ከተማ የጨዋታውን የመጀመርያ የግብ ሙከራ አድርጓል፡፡ ታከለ አለማየሁ ከመስመር ያሻማውን ኳስ ሻኪሩ በግንባሩ ገጭቶ የግቡን አግዳሚ ታኮ ወደ ውጪ ወጥቶበታል፡፡

card_yellow 24′ መሳይ ማልያውን አውልቆ ደስታውን በመግለጹ የጨዋታውን የመጀመርያ ማስጠንቀቅያ ካርድ ተመልክቷል፡፡

 

cb5a1f78247d0a65650169ebbe0e77af8c619332e59a7b232c7d6476799611fb_ originalጎልልል!!!!! ወላይታ ድቻ

24′ መሳይ አንጪሶ በግምት ከ20 ሜትር ርቀት አክርሮ የመታው ኳስ በጃኮብ ፔንዛ መረብ ላይ አርፏል፡፡ መሳይ ማልያውን አውልቆ በመጨፈር ላይ ይገኛል፡፡ ግሩም ግብ!!!

21′ አናጋው ባደግ ከመስመር ያሻገረለትን ኳስ አላዛር በግንባሩ ገጭቶ ወደ ግብ ቢሞክርም ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቶበታል፡፡

20′ ጨዋታው ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ እየተደረገበት ነው፡፡ አናጋው ከሞከረው ሙከራ ውጪ በሁለቱም ቡድኖች መካከል ጥሩ የግብ ማግባት እንቅስቃሴ አልታየም፡፡ ከወላይታ ድቻ በኩል በድሉ መርድ መልካም እቅስቃሴ እያሳየ ነው፡፡

13ወንድወሰን የህክምና እርድታ ተደርጎለት ወደ ጨዋታው ተመልሷል፡፡ ጨዋታውም ለ3 ደቂቃ ተስተጓጉሎ አሁን ተጀምሯል፡፡

9′ ወንድወሰን አሸናፊ ከሚካኤል ጆርጅ ጋር ተጋጭቶ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ የህክምና እርዳታ እየተደረገለትም ይገኛል፡፡ ምናልባትም የወላይታ ድቻ የመጀመርያ የተጫዋች ቅያሪ ሊፈፀም ይችላል፡፡

7′ አናጋው ባደግ ጥሩ የግብ ማግባት አጋጣሚ አግኝቶ ጃኮብ ፔንዛ አድኖበታል፡፡

whistle-5121′ ጨዋታው ሰአቱ 09፡03 ሲል ተጀመረ

 

08:55 የሁለቱም ቡድን ተጫዋቾች እንዲሁም ጨዋታውን የሚመሩት ዳኞች በማማሟቅ ላይ ይገኛሉ፡፡


soccer-4-iconየወላይታ ድቻ አሰላለፍ
ወንድወሰን አሸናፊ
አናጋው ባደግ – ሙባረክ ሽኩሪ – ቶማስ ስምረቱ – ፈቱዲን ጀማል
አማኑኤል ተሾመ – ዮሴፍ ደንጌቶ – በድሉ መርዕድ – ፀጋዬ ብርሃኑ – መሳይ አንጪሶ
አላዛር ፋሲካ


soccer-4-iconየአዳማ ከተማ አሰላለፍ
ጃኮብ ፔንዛ
እሸቱ መና – ወንድወሰን ሚልኪያስ – ሞገስ ታደሰ – ተስፋዬ በቀለ
ዮናታን ከበደ – ፋሲካ አስፋው – ታከለ አለማየሁ
ሚካኤል ጆርጅ – ታፈሰ ተስፋዬ – አቢኮዬ ሻኪሩ


 

ያጋሩ