​መቐለ 70 እንደርታ ጉዳይ ወደ ካፍ አምርቷል

በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ ተሳታፊ ለሆነው መቐለ 70 እንደርታ ጉዳይ መፍትሄ ያስገኛል የተባለ ደብዳቤ ወደ ካፍ ተልኳል።

የ2011 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊው ክለብ መቐለ 70 እንደርታ በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ ከሊቢያው አህሊ ቤንጋዚ ጋር የመጀመርያ ዙር ጨዋታውን መደልደሉ ይታወቃል። በዚህ ሳምንት መጨረሻ ላይ ከኅዳር 18 – 20 ባሉት ቀናት ከሜዳው ውጭ ግብፅ አልያም ቱኒዚያ ላይ የሚጫወት መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። የመልሱን ጨዋታ ከአንድ ሳምንት በኃላ በሜዳው ከኅዳር 25-27 ባሉት ቀናት እንደሚያደርግ መርሐግብር መውጣቱ ይታወቃል። ሆኖም አሁን ባለው ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ አንፃር መቐለ 70 እንደርታን በጨዋታው ላይ እንዲካፈል ለማድረግ ለካፍ ደብዳቤ ተልኳል።

የደብዳቤው ዋና ሀሳብ ዝርዝር መረጃ ያገኘን ባይሆንም አዲስ አበባ የሚገኙትን አስራ አንድ ተጫዋቾችን በመያዝ ወደ ሥፍራው በማቅናት ጨዋታውን እንዲያደርጉ ፍቃድ ስለመጠየቅ እንደሆነ ተገምቷል።
ተስፋ የተጣለበት ይህን ጉዳይ ካፍ ውሳኔው ምን እንደሆነ ዛሬ ሌሊት አልያም ነገ ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

©ሶከር ኢትዮጵያ