ወልቂጤ ከተማ ሁለት ተጫዋቾችን ለማስፈረም ተስማማ
የመሐል ተከላካዩቹ አሌክስ ተሰማ እና አሚኑ ነስሩ ወልቂጤ ከተማን ለመቀላቀል ተስማሙ፡፡
በዘንድሮው የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ላይ የመሳተፋቸው ጉዳይ ያከተመ የሚመስለው የትግራይ ክልል ክለቦች ተጫዋቾች ወደተለያዩ ክለቦች እያመሩ ይገኛሉ። በእነኚህ ክለቦች ውስጥ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል የሆኑት አሌክስ ተሰማ እና አሚኑ ነስሩ ከሰሞኑ ከወልቂጤ ከተማ ጋር ልምምድ እየሰሩ የሚገኝ ሲሆን በጥቂት ቀናትም ውስጥ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ አሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው በተለይ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ከዳሽን ከለቀቀ በኋላ ያለፉትን አምስት ዓመታት በመቐለ 70 እንደርታ ቆይታ የነበረውና ዘንድሮ ለስሑል ሽረ ለመጫወት ፊርማውን አኑሮ የነበረው ተከላካዩ አሌክስ እና ከጅማ አባጅፋር ወደ መቐለ ተጉዞ ከክለቡ ጋር ያለፉትን ሁለት ዓመታት ጥሩ ቆይታ ያደረገው ሌላኛው ተከላካይ አሚኑ ነስሩ በቀጣይ ቀናት የወልቂጤ ከተማ ተጫዋቾች መሆናቸው ዕርግጥ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...