ወልቂጤ ከተማ ሁለት ተከላካዮችን አስፈረመ
የመቐለ 70 እንደርታ ሁለት ተከላካዮች በአንድ ዓመት ውል ሠራተኞቹን ተቀላቅለዋል፡፡
አዲስ አበባ ከትመው ለ2013 ቢትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ዝግጅታቸውን መሥራት ከጀመሩ ወራት ያስቆጠሩት ወልቂጤ ከተማዎች ሁለት ተከላካዮችን በይፋ አስፈርመዋል፡፡ አንጋፋው ተከላካይ ሥዩም ተስፋዬ አዲሱ የክለቡ ፈራሚ ሆኗል፡፡ የቀድሞው የኤሌክትሪክ፣ ደደቢት እና ከ2010 ጀምሮ ለመቐለ 70 እንደርታ እየተጫወተ የቆየው እንዲሁም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም አይረሴ ጊዜን ያሳለፈው ተከላካዩ የመቐለ 70 እንደርታን በሊጉ ያለመሳተፍ ተከትሎ ወደ ወልቂጤ አምርቷል፡፡
ሌላኛው ፈራሚ አሚኑ ነስሩ ነው፡፡ የቀድሞው የሀዲያ ሆሳዕና፣ ጅማ አባጅፋር እና መቐለ ተከላካይ ከሰሞኑ ከወልቂጤ ከተማ ጋር ልምምድ ሲሰራ ከቆየ በኃላ በዛሬው ዕለት በይፋ የክለቡ ተጫዋች መሆኑን ፌድሬሽን በመገኘት አፅድቋል፡፡
ክለቡ ሌላኛው ተከላካይ አሌክስ ተሰማን ለማስፈረም አቅዶ ተጫዋቹም ልምምድ ሲሰራ ከሰነበተ በኃላ ምርጫውን ወደ ሌላ ክለብ በማድረጉ ሳይፈርም መቅረቱን የክለቡ አሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...