ሽመልስ በቀለ መድመቁን ቀጥሏል
ኢትዮጵያዊው አማካይ ሽመልስ በቀለ በግብፅ ፕሪምየር ሊግ በተከታታይ ጎል ማስቆጠሩን ቀጥሏል።
በ11ኛ ሳምንት የግብፅ ፕሪምየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ዋዲ ዴግላን የገጠመው ምስር ለል ማቃሳ 3-1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ደረጃውን ማሻሻል ችሏል። ካይሮ ላይ አመሻሹን በተደረገው በዚህ ጨዋታ ሽመልስ በቀለ በ23ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል ቡድኑን ቀዳሚ ሲያርግ በጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ፓውሊን ቮአቪ እና ባሰም ሞርሲ ላስቆጠሯቸው ጎሎችም አመቻችቶ በማቀበል ድንቅ ዕለት አሳልፏል።
ድሉን ተከትሎ አስራ አራት ጨዋታዎች ያደረገው ምስር ሦስተኛ ተከታታይ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን 23 በማድረስ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ጎል ያስቆጠረው ሽመልስ በቀለም ከዛማሌኩ የሱፍ ኦባማ በመቀጠል በስድስት ጎሎች በከፍተኛ ጎል አስቆጣሪዎች ሰንጠረዥ ሁለተኛ ላይ ተቀምጧል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...