የከፍተኛ ሊጉ ሁለተኛ ዙር የሚደረግባቸው ስፍራዎች እና የዝውውር ቀናት ይፋ ተደርጓል
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድቦች የመጀመርያ ዙር እስከ ቀጣይ ሳምንት ሲጠናቀቅ የሁለተኛ ዙር የሚጀምርበት ጊዜ እና የሚካሄድበት ስፍራ ታውቋል።
በ2013 ውድድር ዓመት ባቱ (ዝዋይ) በሚገኘው የሼር ኢትዮጵያ ስታዲየም፣ በሀዋሳ አርቲፊሻል ሳር ሜዳ እንዲሁም በድሬዳዋ ስታዲየም እየተከናወነ የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል። የምድብ ሀ አስቀድሞ ሲጠናቀቅ የምድብ ለ ሁለት ሳምንታት፣ የምድብ ሐ ደግሞ አንድ ሳምንት መርሐ ግብር ካከናከኑ በኋላ የመጀመርያው ዙር ውድድር ሙሉ ለሙሉ የካቲት 15 ይጠናቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አወዳዳሪው አካል ትናንት ለቡድኖች በላከው ደብዳቤ የምድብ ሀ በሀዋሳ፣ የምድብ ለ በወልዲያ እንዲሁም የምድብ ሐ በነቀምቴ ከተሞች ውድድራቸውን እንዲያከናውኑ ተገልጿል።
የሦስቱም ምድቦች የተጫዋቾች ዝውውር የሚደርጉበት ቀን ይፋ የሆነ ሲሆን ከየካቲት 23 እስከ መጋቢት 13 ድረስ ዝውውሩን እንዲከናውኑ ተወስኗል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...