ሰበታ ከተማ ጋናዊ አጥቂ ለማስፈረም ተስማምቷል
በአሠልጣኝ አብርሃም መብራቱ የሚመሩት ሰበታ ከተማዎች በዘንድሮ የውድድር ዓመት የመጀመሪያ የውጪ ዜጋ ተጫዋቾቻቸውን ወደ ስብስባቸው ለመቀላቀል ተስማምተዋል።
በዘንድሮ የውድድር ዓመት አንድም የውጪ ዜጋ ተጫዋች ሳያስፈርሙ ሊጉን የጀመሩት ሰበታ ከተማዎች የአጥቂ ክፍላቸውን ለማጠናከር ወደ ዝውውር ገበያው ገብተዋል። በዚህም የቀድሞ የመቐለ 70 እንድርታ እና ፋሲል ከነማ ተጫዋች የነበረው ኦሲ ማውሊን ወደ ስብስባቸው ለመቀላቀል የቅድመ ስምምነት ፈፅመዋል።
ይህ ጋናዊ የአጥቂ መስመር ተጫዋች 2011 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ከመቐለ 70 እንድርታ ጋር ድንቅ ጊዜን በማሳለፍ የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱ ይታወሳል። በተሰረዘው የውድድር ዘመንም ወደ ፋሲል ከነማ በመጓዝ ግልጋሎት ሲሰጥ ቆይቷል። በዛሬው ዕለት ደግሞ ተጫዋቹ ሶስተኛ የኢትዮጵያ ክለቡን ለመቀላቀል ቅድመ ስምምነት መፈፀሙን ሶከር ኢትዮጵያ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...