ሴቶች ፕሪምየር ሊግ | አዲስ አበባ ከተማ አሰልጣኟን አገደ
በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አንደኛ ዲቪዚዮን ተሳታፊ የሆነው አዲስ አበባ ከተማ ዋና አሰልጣኙ ሙሉጎጃም እንዳለን ለስድስት ወራት አገደ ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ከሰሞኑ ባደረጉት ከፍተኛ ግምገማ ከ2012 ጀምሮ ቡድኑን በዋና አሰልጣኝነት ስትመራ የቆየችው ሙሉጎጃም እንዳለን ለስድስት ወራት ከክለቡ አሰልጣኝነት አግዷል፡፡ በስምንት ነጥቦች 7ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አአ ከተማ ከውጤት መጥፋት በተጨማሪ ስፖርተኞችን መከፋፈል፣ በአግባቡ አለመምራት፣ ከስፖርተኞች ጋር አብሮ ማደር እንዲሁም ጥቅምን ከተጫዋቾቹ መቀበል፣ የቡድኑ ረዳት አሰልጣኝ እና ቡድን መሪ ላይ ዛቻን ማሳደርን የመሳሰሉ ችግሮችን በአሰልጣኟ ላይ በመመልከቱ እግድ ማስተላለፉን ክለቡ ገልጿል፡፡
በአዳማ እየተደረገ በሚገኘው የሁለተኛው ዙር የሴቶች ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ የሆነው አዲስ አበባ እስከ ውድድሩ ማብቂያ ድረስ በረዳት አሰልጣኟ የሺሀረግ ለገሰ እንዲሁም ሦስተኛ አሰልጣኝ በነበረው አሳምነው ገብረወልድ ጊዜያዊ አሰልጣኝነት እንደሚመራ የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ ነፃነት ለድረገፃችን ተናግረዋል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...