የከፍተኛ ሊጉ ክለብ የመኪና አደጋ ገጠመው
በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እየተሳተፈ የሚገኘው ክለብ የመኪና አደጋ ማስተናገዱ ተሰምቷል።
በድሬዳዋ ሲደረግ በነበረው የከፍተኛ ሊግ የምድብ ሐ ውድድር ተሳታፊ በመሆን የአንደኛውን ዙር ያጠናቀቀው የነገሌ አርሲ ክለብ በዛሬው ዕለት ቡድኑን ይዞ ሲጓዝ የነበረው መኪና አደጋን ማስተናገዱ ታውቋል፡፡ ቡድኑ ውድድሩን አጠናቆ በዛሬው ዕለት ከድሬዳዋ ወደ ነገሌ አርሲ ከተማ ሲያመራ አዳማ መግቢያ ላይ ተጫዋቾቹን እና የቡድኑን አባላት የያዘው መኪና አደጋ አስተናግዷል፡፡ መንገድ ስቶ የመጣን ተሳቢ መኪና አድናለው በማለት ተጫዋቾቹን የያዘው ሹፌር የመሪውን አቅጣጫ ሲቀይር አደጋው ሊከሰት እንደቻለም ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች፡፡ በአደጋው አንድ የቡድኑ ተጫዋች መጠነኛ ጉዳት በማስተናገዱ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ያመራ ሲሆን ሌሎች የቡድኑ የአሠልጣኝ አባላት እና ተጫዋቾች በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙም ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡
በተመሳሳይ በቅርቡ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ አንደኛ ዲቪዚዮን ተካፋይ የሆነው የአርባምንጭ ከተማ የሴቶች ክለብ የመኪና አደጋን ማስተናገዱ ይታወሳል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...