ዋልያዎቹ የአቋም መለኪያ ጨዋታ ለማግኘት ተቃርበዋል
ካሜሩን ለምታስተናግደው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የምድብ የማጣሪያ ጨዋታቸውን እያደረጉ የሚገኙት ዋልያዎቹ ከሁለት ሀገራት ጋር የአቋም መለኪያ ጨዋታ ለማድረግ ንግግር ላይ መሆናቸው ታውቋል።
በአሠልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከኮትዲቯር፣ ማዳጋስካር እና ኒጀር ጋር ተደልድሎ የምድብ የማጣሪያ ጨዋታውን እያደረገ ይገኛል። ካከናወናቸው አራት ጨዋታዎች ስድስት ነጥቦችን በመያዝ የምድቡ አምስተኛ እና ስድስተኛ ጨዋታዎቹን በመጠባበቅ ላይ የሚገኘው ቡድኑ ከጨዋታዎቹ በፊት ጠንካራ የአቋም መለኪያ ጨዋታ ለማድረግ እየጣረ ይገኛል። ሶከር ኢትዮጵያ እንዳገኘው መረጃ ከሆነ ደግሞ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከመጋቢት አጋማሽ ጀምሮ ከሚደረጉት ወሳኝ ጨዋታዎች በፊት ከማላዊ እና ታንዛኒያ ብሔራዊ ቡድኖች ጋር ቡድኑ እንዲጫወት እየጣረ ይገኛል።
በምድብ 11 የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በነጥብ (7) እኩል ሆነው በእርስ በእርስ ግንኙነት በተበላለጡት ኮትዲቯር እና ማዳጋስካር ተበልጦ የምድቡ ሦስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...