ጅማ አባጅፋር ተጫዋች ለማስፈረም ተስማምቷል
በቅርቡ አዲስ አሠልጣኝ የሾሙት ጅማ አባጅፋሮች አንድ ተጫዋች ወደ ስብስባቸው ለመቀላቀል ቅድመ ስምምነት ፈፅመዋል።
የ2010 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ክለብ የሆነው ጅማ አባጅፋር በዘንድሮ የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ባሳየው ደካማ ብቃት የወራጅ ቀጠናው ቦታ ላይ ይገኛል። የክለቡ አመራሮችም ከአሠልጣኝ ጻውሎስ ጋር ከተለያዩ በኋላ በሊጉ ልምድ ያላቸውን አሠልጣኝ ፀጋዬን በመሾም ካሉበት ወራጅ ቀጠና ለመውጣት እየጣሩ ይገኛሉ። አሠልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምም ቡድኑ በሁለተኛው ዙር ተጠናክሮ እንዲቀርብ በዛሬው ዕለት አንድ ተጫዋች ወደ ስብስባቸው ለመቀላቀል መስማማታቸው ተረጋግጧል።
ቡድኑን ለመቀላቀል የተስማማው ተጫዋች አማኑኤል ተሾመ ነው። የቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ፣ ወላይታ ዲቻ፣ መከላከያ እና ድሬዳዋ ከተማ ተጫዋች የነበረው የተከላካይ አማካዩ አማኑኤል ያለፉትን ስድስት ወራት ዳግም ወደ ወላይታ በማምራት መጫወቱ ይታወሳል። ተጫዋቹም በሊጉ በርካታ ግቦችን እያስተናገደ ለሚገኘው የቡድኑ የተከላካይ መስመር ሽፋን በመስጠት ቡድኑን ያጠናክራል ተብሎ ይገመታል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...
የአሠልጣኞች አስተያየት | ባህር ዳር ከተማ 1-0 ድሬዳዋ ከተማ
በወራጅ ቀጠናው ትልቅ ትርጉም ያለው ፍልሚያ በጣናው ሞገዶቹ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ የአሸናፊ ቡድን አሠልጣኝ አስተያየት ሲሰጡ የተሸናፊው ግን ፍቃደኛ ሳይሆኑ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች
የሳምንቱን ፍልሚያዎች የሚያስጀምሩት የነገ ሁለት መርሐ-ግብሮች እንደሚከተለው ዳሰናል። ባህር ዳር ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ በ26ኛ ሳምንት በሀዋሳ ከተማ እና አርባምንጭ...
ፌዴሬሽኑ የሻረውን ኃላፊነት ለሊግ ካምፓኒው መልሶ ሰጥቷል
ከሰሞኑ ውዝግብ ውስጥ ገብተው የነበሩት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር ወደ ስምምነት መጥተዋል። የወልቂጤ ከተማው አምበል ጌታነህ...