ወላይታ ድቻ ከናይጄሪያዊው አጥቂ ጋር ተስማምቷል
ወላይታ ድቻ ናይጄሪያዊውን የቀድሞ የፋሲል አጥቂ ለማስፈረም ተስማምቷል።
የመሐል እና የመስመር አጥቂው ኢዙ አዙካ ድቻን የተቀላቀለ ተጫዋች ነው። የህንዱ ክለብ ጃምሼድፑርን ከሁለት ዓመት በፊት ለቆ 2011 ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በፋሲል ከነማ እስከተሰረዘው የውድድር ዓመት ድረስ መጫወት የቻለው ኢዙ ከዐፄዎቹ ጋር ኮንትራቱ ከተጠናቀቀ በኃላ ጥቂት ጊዜን ካለ ክለብ አሳልፎ ወደ ወላይታ ድቻ ለማምራት ቀደም ብሎ ንግግር ጀምሮ የነበረ ሲሆን አሁን ክለቡን ለመቀላቀል ተስማምቷል። የአጥቂ እጥረት ያለበትን ቡድን እንደሚያጠናክርም ይጠበቃል።
ወላይታ ድቻ ከኢዙ በፊት አስናቀ ሞገስ፣ ነፃነት ገብረመድህን፣ ዮናስ ግርማይ፣ ዳንኤል አጃይ፣ ዲዲዬ ለብሪ እና ጋቶች ፓኖምን ለማስፈረም የተስማማ ሲሆን ከስድስት ተጫዋቾች ጋር ደግሞ ተለያይቷል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...