አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርሟል
በትላንትናው ዕለት ኤልያስ ማሞን ያስፈረሙት አዳማ ከተማዎች በዛሬው ዕለት ተጨማሪ ሁለት ተጫዋቾችን ወደ ቡድናቸው ቀላቅለዋል።
በሁለተኛ ዙር የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ተጠናክረው ለመቅረብ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙት አዳማ ከተማዎች የአሠልጣኝ ለውጥ ካደረጉ በኋላ ፊታቸውን ወደ ተጫዋቾች ዝውውር አዙረዋል። በዚህም የአጥቂ አማካዩን ኤልያስ ማሞን በትላንትናው ዕለት ማስፈረማቸውን መዘገባችን ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ የቡድኑ አሠልጣኝ ዘርዓይ ሁለት ተጫዋቾችን ማስፈረማቸው ታውቋል።
ቡድኑን የተቀላቀለው የመጀመሪያው ተጫዋች ሀብታሙ ወልዴ ነው። ይህ የቀድሞ የኢትዮጵያ መድን፣ መከላከያ እና ድሬዳዋ ከተማ የአጥቂ መስመር ተጫዋች የሊጉን ሦስተኛ ደካማ አጥቂ ቡድን ለማጠናከር አዳማ ደርሷል። በዚህም የቡድኑን የአጥቂ መስመር ከአብዲሳ ጀማል ጋር በመፎካከር ለማጠናከር እንደሚጥር ይገመታል።
ሁለተኛው ለአዳማ ፊርማውን ያኖረው ተጫዋች ሚሊዮን ሰለሞን ነው። የቀድሞ የሀምበሪቾ፣ አዲስ አበባ ከተማ እና ሲዳማ ቡና የመስመር ተከላካይ የነበረው ሚሊዮን የቀድሞ አሠልጣኙ ዘርዓይ ሙሉን በመከተል መዳረሻውን አዳማ አድርጓል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...