ቡርትካናማዎቹ ሁለት ተጨማሪ ተጫዋቾችን የግላቸው አድርገዋል
ከሰዓታት በፊት ሄኖክ ገምቴሳን ያስፈረሙት ድሬዳዋ ከተማዎች አሁን ደግሞ ሁለት ተጨማሪ ተጫዋች ወደ ቡድናቸው ቀላቅለዋል።
ቡድኑን የተቀላቀለው የመጀመሪያው ተጫዋች ዐወት ገብረሚካኤል ነው። ከኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድን የተገኘው የቀኝ መስመር ተከላካዩ ዐወት አሳዳጊ ክለቡን ካገለገለ በኋላ ወደ ጅማ አባጅፋር ቀጥሎም ወደ ስሑል ሽረ አምርቶ መጫወቱ ይታወሳል። ባለፈው የውድድር ዓመት ሊጉ ከመቋረጡ በፊት ወደ ወልዋሎ አምርቶ የነበረው ተጫዋቹ በክልሉ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ግማሹን ዓመት ሳይጫወት ቆይቶ አሁን ብርቱካናማዎቹን ተቀላቅሏል።
ሁለተኛው አዲስ ተጫዋች የግብ ዘቡ ወንድወሰን አሸናፊ ነው። የቀድሞ የሙገር፣ ወላይታ ድቻ፣ ኢትዮጵያ ቡና እና ስሑል ሽረ ግብ ጠባቂ ወደ ወልዋሎ አምርቶ የነበረ ቢሆንም የትግራይ ክልል ክለቦች በሊጉ አለመሳተፋቸውን ተከትሎ በዘንድሮ የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ መጫወት ሳይችል ቀርቶ ነበር። አሁን ግን መዳረሻው የምስራቁ ክለብ ድሬዳዋ ሆኗል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...
የአሠልጣኞች አስተያየት | ባህር ዳር ከተማ 1-0 ድሬዳዋ ከተማ
በወራጅ ቀጠናው ትልቅ ትርጉም ያለው ፍልሚያ በጣናው ሞገዶቹ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ የአሸናፊ ቡድን አሠልጣኝ አስተያየት ሲሰጡ የተሸናፊው ግን ፍቃደኛ ሳይሆኑ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች
የሳምንቱን ፍልሚያዎች የሚያስጀምሩት የነገ ሁለት መርሐ-ግብሮች እንደሚከተለው ዳሰናል። ባህር ዳር ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ በ26ኛ ሳምንት በሀዋሳ ከተማ እና አርባምንጭ...
ፌዴሬሽኑ የሻረውን ኃላፊነት ለሊግ ካምፓኒው መልሶ ሰጥቷል
ከሰሞኑ ውዝግብ ውስጥ ገብተው የነበሩት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር ወደ ስምምነት መጥተዋል። የወልቂጤ ከተማው አምበል ጌታነህ...