አዳማ ከተማ ሁለት ተጨማሪ ተጫዋቾችን አስፈረመ
አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉን የሾመውና ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት አልሞ ዝውውር እያደረገ የሚገኘው አዳማ ከተማ ተጨማሪ ሁለት ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል።
ኤልያስ አሕመድ ከፈራሚዎቹ መካከል ነው። የቀድሞው የሰበታ ከተማ፣ ባህር ዳር ከተማ እና ጅማ አባ ጅፋር አማካይ በዚህ የውድድር ዓመት ወደ ወላይታ ድቻ በማምራት ግማሽ ዓመት ያሳለፈ ሲሆን ከቀናት በፊት ከክለቡ ጋር ተያይቶ ወደ አዳማ ከተማ አቆንቷል።
ያሬድ ብርሀኑ ሌላው የአዳማ አዲስ ተጫዋች ነው። ከትራንስ ኢትዮጵያ ቢ ቡድን ከተገኘ በኋላ በደደቢት፣ ወልዲያ እንዲሁም በሁለት አጋጣሚ ለመቐለ 70 እንደርታ መጫወት የቻለው ይህ ፈጣን ተጫዋች መቐለን በተሰረዘው የውድድር አጋማሽ ከለቀቀ በኃላ ለወልዋሎ ለመጫወት የተስማማ ቢሆንም ክለቡ በፕሪምየር ሊጉ አለመሳተፉን ተከትሎ ጥቂት ወራት ካለ ክለብ ከቆየ በኃላ አዳማ ከተማን ተቀላቅሏል።
ሁለቱን ጨምሮ ስድስት አዳዲስ ተጫዋቾችን የቀላቀለው አዳማ ከተማ በቀጣይ ከስምንት ተጫዋቾች ጋር ይለያያል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...