አሚኑ ነስሩ አዲስ ክለብ ለመቀላቀል ተስማምቷል
ከሳምንታት በፊት ከወልቂጤ ከተማ ጋር በስምምነት የተለያየው የሁለት ጊዜ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊው ተጫዋች አሚኑ አዲስ ክለብ ለመቀላቀል ተስማምቷል።
የቀድሞ የጅማ አባጅፋር እና መቐለ 70 እንድርታ የኋላ ደጀን የነበረው አሚኑ ነስሩ በያዝነው የውድድር ዓመት ወደ ሠራተኞቹ አምርቶ ለመጫወት ፊርማው አኖሮ እንደነበር ይታወሳል። ሆኖን ግን ከጥቂት ሳምንታት በፊት ተጫዋቹ እና ክለቡ ተስማምተው ተጫዋቹ ራሱን ነፃ አድርጎ ነበር። አሁን ሶከር ኢትዮጵያ ባገኘችው መረጃ ከሆነ ደግሞ ተጫዋቹ አዳማ ከተማን ለመቀላቀል ቅድመ ስምምነት ፈፅሟል።
በተከታታይ ሁለት ዓመታት (2010 እና 2011) የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ዋንጫ ከጅማ እና መቐለ ጋር ያነሳው አሚኑ በዘንድሮ የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ በርካታ ግቦችን (26) ካስተናገዱ ክለቦች መካከል ቀዳሚው የሆነውን አዳማን የመከላከል አቅም ያሳድጋል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...
የአሠልጣኞች አስተያየት | ባህር ዳር ከተማ 1-0 ድሬዳዋ ከተማ
በወራጅ ቀጠናው ትልቅ ትርጉም ያለው ፍልሚያ በጣናው ሞገዶቹ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ የአሸናፊ ቡድን አሠልጣኝ አስተያየት ሲሰጡ የተሸናፊው ግን ፍቃደኛ ሳይሆኑ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች
የሳምንቱን ፍልሚያዎች የሚያስጀምሩት የነገ ሁለት መርሐ-ግብሮች እንደሚከተለው ዳሰናል። ባህር ዳር ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ በ26ኛ ሳምንት በሀዋሳ ከተማ እና አርባምንጭ...
ፌዴሬሽኑ የሻረውን ኃላፊነት ለሊግ ካምፓኒው መልሶ ሰጥቷል
ከሰሞኑ ውዝግብ ውስጥ ገብተው የነበሩት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር ወደ ስምምነት መጥተዋል። የወልቂጤ ከተማው አምበል ጌታነህ...