ነብሮቹ የአማካያቸውን ውል አድሰዋል
በአሠልጣኝ አሸናፊ በቀለ የሚመሩት ሀዲያ ሆሳናዎች የወሳኝ አማካያቸውን ውል አራዝመዋል።
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አራተኛ ደረጃን ይዘው በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ አለሁ የሚሉት ሀዲያ ሆሳዕናዎች ከቀናት በፊት የመድሃኔ ብርሃኔን ውል ማደሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል። በሊጉ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ የቀረበው ቡድኑ በዛሬው ዕለት ደግሞ የተስፋዬ አለባቸውን ውል ማራዘሙ ታውቋል።
የቀድሞ የሰበታ ከተማ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ወልድያ እና ወላይታ ዲቻ ተጫዋች የነበረው ተስፋዬ በዘንድሮ የሊግ ውድድር ጥሩ ግልጋሎቱን ለክለቡ እየሰጠ ይገኛል። የተጫዋቹ ውሉን ማደስም ለአሠልጣኝ አሸናፊ በቀለ ጥሩ ዜና መሆኑ ይገመታል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...