ዋልያዎቹ የአቋም መለኪያ ጨዋታ ያደርጋሉ
ሁለት ወሳኝ የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች ከፊታቸው የሚጠብቃቸው ዋልያዎቹ አንድ የአቋም መለኪያ ጨዋታ ማግኘታቸውን ይፋ ሆኗል።
በአሠልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ 11 ከኮተዲቯር፣ ኒጀር እና ማዳጋስካር ጋር ተደልድሎ ለካሜሩኑ የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የማጣሪያ ጨዋታዎችን እያደረገ ይገኛል። ከመጋቢት ወር አጋማሽ ጀምሮም የምድቡ አምስተኛ እና ስድስተኛ ጨዋታውን ባህር ዳር እና አቢጃን ላይ ከማዳጋስካር እና ኮትዲቯር ጋር ያከናውናል።
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንም ከሁለቱ ወሳኝ ጨዋታዎች በፊት ቡድኑ የአቋም መለኪያ ጨዋታ እንዲያገኝ ከታንዛኒያ እና ማጋዊ ጋር ንግግር ሲያደርግ እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል። አሁን ይፋ በሆነ መረጃም መጋቢት 8 ከማላዊ አቻው ጋር በባህር ዳር ዓለማቀፍ ስታዲየም ጨዋታ እንደሚያደርግ ይፋ ተደርጓል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...