ቢንያም በላይ ወደ ኢትዮጵያ የሚመልሰውን ዝውውር ለመፈፀም ተስማማ
በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰው የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ ቢንያም በላይ በፕሪምየር ሊጉ የሚገኝ ክለብን ለመቀላቀል ተስማምቷል።
ባለ ተስጥኦው የቀድሞው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አማካይ ቢኒያም በላይ አሳዳጊ ክለቡ ንግድ ባንክን በ2009 ለቆ ወደ ጀርመን በማቅናት ለዳይናሞ ደርስደን ለመጫወት የሙከራ ጊዜ ካሳለፈ በኋላ ወደ አልባንያ በማምራት ከስከንደርቡ ክለብ ጋር ሁለት ስኬታማ ዓመታት አሳልፏል፡፡ በአልባኒያ ቆይታው የሊጉን ዋንጫ ከቡድኑ ጋር ካነሳ በኃላ በመቀጠልም በስዊድኖቹ ክለቦች ስሪያንስካ እና ኡመያ ክለቦች በመጫወት ቆይታን አድርጓል፡፡
የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ ከሳምንታት በፊት ወደ ሀገሩ ኢትዮጵያ የተመለሰ ሲሆን በዚህ የዝውውር መስኮት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ክለቦች እንደሚዘዋወር ሲጠበቅ ቆይቷል። በዚህም ሲዳማ ቡናን ለመቀላቀል ከስምምነት መድረሱን እና አዲስ ነገር ካልተፈጠረ በቀር ለቡድኑ ፊርማውን አኑሮ ወደ ባህር ዳር በማቅናት ቡድኑን ለመቀላቀል እንደተዘጋጀ ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።
ከውጤት ቀውስ ለመውጣት በዝውውር መስኮቱ እየተሳተፈ የሚገኘው ክለቡ ተጨማሪ አዲስ ፈራሚዎችን እንደሚቀላቅል እና በምትኩ ከበርካታ ተጫዋቾች ጋር እንደሚለያይ ይጠበቃል።
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ29ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች
የነገውን ተጠባቂ የጨዋታ ቀን የተመለከተው ዳሰሳችን እንዲህ ይነበባል። ወደ ፍፃሜው እየቀረበ በሚገኘው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ነገ እጅግ አጓጊ የሆነ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...